በአገልግሎት ውጤታማ ለመሆን ተጣጣር | በአገልግሎት የምታገኙትን ደስታ አሳድጉ
ጥያቄዎችን ተጠቀሙ
“ደስተኛው አምላክ” ይሖዋ በአገልግሎታችን ደስታ እንድናገኝ ይፈልጋል። (1ጢሞ 1:11) ክህሎታችንን ለማሳደግ ጥረት ባደረግን መጠን ደስታችንም ይጨምራል። ጥያቄ መጠየቅ የሰዎችን የማወቅ ፍላጎት ለመቀስቀስ እንዲሁም በቀላሉ ውይይት ለመጀመር ያስችላል። ጥያቄዎች ሰዎች እንዲያስቡና እንዲያመዛዝኑ ለማድረግ ይረዳሉ። (ማቴ 22:41-45) ጥያቄ መጠየቃችንና ግለሰቡ መልስ ሲሰጥ ማዳመጣችን ለግለሰቡ ትልቅ ቦታ እንደምንሰጠው ያሳያል። (ያዕ 1:19) ግለሰቡ የሚሰጠው መልስ ውይይቱን እንዴት መቀጠል እንዳለብን ለመወሰን ሊረዳን ይችላል።
ደቀ መዛሙርት የማድረጉ ሥራ የሚያስገኘውን ደስታ አጣጥሙ—ክህሎታችሁን አሻሽሉ—ጥያቄዎችን መጠቀም የሚለውን አጭር ድራማ ተመልከት፤ ከዚያም የሚከተሉትን ጥያቄዎች ለመመለስ ሞክር፦
-
ጄድ የትኞቹን መልካም ባሕርያት አሳይታለች?
-
ኒታ ለጄድ ትኩረት እንደሰጠቻት ለማሳየት ጥያቄዎችን የተጠቀመችው እንዴት ነው?
-
ኒታ ጄድ ለምሥራቹ ፍላጎት እንዲኖራት ለመርዳት ጥያቄዎችን የተጠቀመችው እንዴት ነው?
-
ኒታ ጄድ እንድታስብና እንድታመዛዝን ለመርዳት ጥያቄዎችን የተጠቀመችው እንዴት ነው?