ክርስቲያናዊ ሕይወት
ከግል ጥናትህ የበለጠ ጥቅም ማግኘት
አስፈላጊ የሆነው ለምንድን ነው? በአምላክ ቃል ላይ የምናደርገው የግል ጥናት የእውነት “ስፋቱ፣ ርዝመቱ፣ ከፍታውና ጥልቀቱ ምን ያህል እንደሆነ” በሚገባ ለመረዳት ያስችለናል። (ኤፌ 3:18) በተጨማሪም በዚህ ክፉ ዓለም ውስጥ እንከንና እድፍ የሌለብን ሆነን እንድንኖር እንዲሁም ‘የሕይወትን ቃል አጥብቀን መያዝ’ እንድንችል ይረዳናል። (ፊልጵ 2:15, 16) የግል ጥናት፣ በግለሰብ ደረጃ የሚያስፈልገንን ትምህርት መርጠን ለማጥናት አጋጣሚ ይሰጠናል። የአምላክን ቃል በማንበብና በማጥናት ከምናሳልፈው ጊዜ፣ የበለጠ ጥቅም ለማግኘት ምን ማድረግ እንችላለን?
ይህን ማድረግ የሚቻለው እንዴት ነው?
-
ለማጥናት በምትጠቀምበት መጽሐፍ ቅዱስ (በታተመውም ሆነ በኤሌክትሮኒክ ፎርማት በተዘጋጀው) ጥቅሶች ላይ ማስመር እንዲሁም ማስታወሻ ማስፈር ጠቃሚ ነው
-
የአምላክን ቃል ስታነብ ‘ማን? ምን? መቼ? የት? ለምን? እንዴት?’ እያልክ ራስህን ጠይቅ
-
የተሟላ መረጃ ለማግኘት ሞክር። በተዘጋጁልን የምርምር መሣሪያዎች ተጠቅመህ በርዕሰ ጉዳይ ወይም በጥቅስ ምርምር አድርግ
-
ትምህርቱን በግልህ እንዴት ተግባራዊ ማድረግ እንደምትችል ለማስተዋል፣ ባነበብከው ነገር ላይ አሰላስል
-
የተማርከውን ነገር በሕይወትህ ተግባራዊ አድርግ።—ሉቃስ 6:47, 48
ውጤታማ የሆነ የግል ጥናት በማድረግ እውነትን ‘አጥብቆ መያዝ’ የሚለውን ቪዲዮ ተመልከት፤ ከዚያም የሚከተሉትን ጥያቄዎች ለመመለስ ሞክር፦
-
አንዳንዶች የግል ጥናትን በተመለከተ ምን ብለዋል?
-
የግል ጥናት ማድረግ ከመጀመራችን በፊት ምንጊዜም መጸለያችን አስፈላጊ የሆነው ለምንድን ነው?
-
አንድን የመጽሐፍ ቅዱስ ዘገባ በደንብ መረዳት እንድንችል ምን ሊያግዘን ይችላል?
-
ለጥናት በምንጠቀምበት መጽሐፍ ቅዱስ ላይ ምን ዓይነት ምልክቶች ማድረግ እንችላለን?
-
የአምላክን ቃል ስናጠና ማሰላሰላችን በጣም አስፈላጊ የሆነው ለምንድን ነው?
-
የተማርነውን ነገር ምን ልናደርግ ይገባል?