ክርስቲያናዊ ሕይወት
ወላጆች—ልጆቻችሁ ይሖዋን ማስደሰት የሚችሉት እንዴት እንደሆነ አስተምሯቸው
ልጆች በይሖዋ ፊት በጣም ውድ ናቸው። ይሖዋ፣ የሚያደርጉትን መንፈሳዊ እድገትና ጽናታቸውን በትኩረት ይመለከታል። (1ሳሙ 2:26፤ ሉቃስ 2:52) በጣም ትናንሽ ልጆችም እንኳ ጥሩ ጠባይ በማሳየት የይሖዋን ልብ ደስ ሊያሰኙት ይችላሉ። (ምሳሌ 27:11) ይሖዋ በድርጅቱ አማካኝነት ወላጆች ልጆቻቸው እሱን እንዲወዱትና እንዲታዘዙት ለማሠልጠን ሊጠቀሙባቸው የሚችሉ ግሩም መሣሪያዎችን አዘጋጅቷል።
ልጆች—መጽናታችሁ የይሖዋን ልብ ደስ ያሰኛል! የሚለውን ቪዲዮ ተመልከት፤ ከዚያም የሚከተሉትን ጥያቄዎች ለመመለስ ሞክር፦
-
ባለፉት ዓመታት ውስጥ ይሖዋ ልጆችን ለማሠልጠን ምን እርዳታና መመሪያ አዘጋጅቷል?
-
በአሁኑ ጊዜ ወላጆች ሊጠቀሙባቸው የሚችሉ ምን መሣሪያዎች አሉ?
-
ልጅ ከሆንክ ይሖዋ ካዘጋጃቸው ዝግጅቶች መካከል አንተን የጠቀመህ የትኛው ነው? እንዲህ ብለህ የመለስከው ለምንድን ነው?