ከአምላክ ቃል የሚገኝ ውድ ሀብት
ሌሎችን ስናጽናና ምን ማድረግ እንደሌለብን ከኤሊፋዝ እንማራለን
ኤሊፋዝ የሰው ልጆች መቼም ቢሆን አምላክን ሊያስደስቱት እንደማይችሉ ለኢዮብ ነግሮታል (ኢዮብ 15:14-16፤ w05 9/15 26 አን. 4-5)
ኤሊፋዝ፣ ኢዮብ ክፉ እንደሆነና መከራ እየደረሰበት ያለው በዚያ ምክንያት እንደሆነ የሚጠቁም ሐሳብ ተናግሯል (ኢዮብ 15:20)
ኤሊፋዝ የተናገራቸው ነገሮች ኢዮብን አላጽናኑትም (ኢዮብ 16:1, 2)
ኤሊፋዝ ለኢዮብ የነገረው ነገር ውሸት ነበር። ይሖዋ እሱን ለማገልገል የምናደርገውን ጥረት ከፍ አድርጎ ይመለከታል። (መዝ 149:4) ጻድቅ የሆኑ ሰዎችም እንኳ ችግር ሊደርስባቸው እንደሚችል ሊጠብቁ ይገባል።—መዝ 34:19
ለማሰላሰል የሚረዳ ጥያቄ፦ ‘የተጨነቁትን ማጽናናት’ የምንችለው እንዴት ነው?—1ተሰ 5:14፤ w15 2/15 9 አን. 16