ክርስቲያናዊ ሕይወት
በቤቴል ያሉትን ለማጽናናት የተደረገ ዝግጅት
ሁሉም ሰው ተፈታታኝ ሁኔታዎች ስለሚያጋጥሙት መጽናኛና ድጋፍ ያስፈልገዋል። በመንፈሳዊ ጠንካራ የሆኑ ወይም ትልቅ የአገልግሎት መብት ያላቸውም እንኳ ተስፋ ሊቆርጡ ይችላሉ። (ኢዮብ 3:1-3፤ መዝ 34:19) ለቤቴል ቤተሰብ አባላት እረኝነት እንዲደረግላቸው ከተደረገው ዝግጅት ምን ትምህርት እናገኛለን?
“በአምላክ ታመኑ” የሚለውን ቪዲዮ ተመልከት፤ ከዚያም የሚከተሉትን ጥያቄዎች ለመመለስ ሞክር፦
-
የቤቴል ቤተሰብ አባላት ምን ተፈታታኝ ሁኔታዎች ያጋጥሟቸዋል?
-
እነሱን ለማጽናናት የትኞቹ አራት ነገሮች ተደርገዋል?
-
መጽናኛ የሚሰጡት ወንድሞች ምን ጥቅም አግኝተዋል?