2 ዮሐንስ 1-13፤ 3 ዮሐንስ 1-14–ይሁዳ 1-25
ከአምላክ ቃል የሚገኝ ውድ ሀብት |እውነት ውስጥ ለመቆየት ብርቱ ተጋድሎ ማድረግ አለብን
ኢየሱስ “በጠባቡ በር ለመግባት ከፍተኛ ተጋድሎ አድርጉ” የሚል ማሳሰቢያ ሰጥቷል። (ሉቃስ 13:24) ኢየሱስ የተናገረው ሐሳብ በአምላክ ዘንድ ተቀባይነት ለማግኘት ብርቱ ትግል ማድረግ እንደሚያስፈልገን ይጠቁማል። የኢየሱስ ወንድም ይሁዳም ‘ለእምነት ብርቱ ተጋድሎ አድርጉ’ በማለት በመንፈስ መሪነት ጽፏል። የሚከተሉትን ነገሮች ለማድረግ ከፍተኛ ጥረት ያስፈልጋል፦
-
ከፆታ ብልግና ለመራቅ።—ይሁዳ 6, 7
-
በኃላፊነት ቦታ ላይ ያሉትን ለማክበር።—ይሁዳ 8, 9
-
“እጅግ ቅዱስ” በሆኑት ክርስቲያናዊ ትምህርቶች ላይ ያለንን እምነት ለማጠናከር።—ይሁዳ 20, 21