በቀጥታ ወደ ዋናው ጉዳይ ግባ

በቀጥታ ወደ ርዕስ ማውጫው ሂድ

ከአምላክ ቃል የሚገኝ ውድ ሀብት | ሮም 9-11

የወይራ ዛፉ ምሳሌ

የወይራ ዛፉ ምሳሌ

11:16-26

የምሳሌያዊው የወይራ ዛፍ የተለያዩ ክፍሎች ምን ያመለክታሉ?

  • ዛፉ፦ አምላክ ከአብርሃም ቃል ኪዳን ጋር በተያያዘ ያለውን ዓላማ አፈጻጸም

  • ግንዱ፦ የአብርሃም ዘር ዋነኛ ክፍል የሆነውን ኢየሱስን

  • ቅርንጫፎቹ፦ በአብርሃም ዘር ሁለተኛ ክፍል ውስጥ የሚካተቱትን ሰዎች ሙሉ ቁጥር

  • “የተሰበሩት” ቅርንጫፎች፦ ኢየሱስን ያልተቀበሉትን ሥጋዊ እስራኤላውያን

  • ‘የተጣበቁት’ ቅርንጫፎች፦ ከአሕዛብ ወገን የሆኑትን ቅቡዓን ክርስቲያኖች

በትንቢት እንደተነገረው የአብርሃም ዘር ማለትም ኢየሱስና 144,000ዎቹ “ለአሕዛብ በረከት” ያስገኛሉ።—ሮም 11:12፤ ዘፍ 22:18

ይሖዋ ከአብርሃም ዘር ጋር በተያያዘ ያለውን ዓላማ የፈጸመበት መንገድ ስለ እሱ ምን ያስተምረኛል?