ከአምላክ ቃል የሚገኝ ውድ ሀብት
“የምድሪቱን ነዋሪዎች በሙሉ ከፊታችሁ አባሯቸው”
ይሖዋ፣ ሕዝቡ ለእሱ በሚያቀርቡት አምልኮ ረገድ መሰናክል የሚሆንባቸውን ማንኛውም ነገር ከተስፋይቱ ምድር እንዲያስወግዱ አዟቸው ነበር (ዘኁ 33:52፤ w10 8/1 23)
ይሖዋ፣ ምድሪቱን ሙሉ በሙሉ ለመቆጣጠር የሚወስዱትን ቆራጥ እርምጃ እንደሚባርክ ነግሯቸው ነበር (ዘኁ 33:53)
እስራኤላውያን ጠላቶቻቸውን ከምድሪቱ ሙሉ በሙሉ አለማባረራቸው ለችግር እንደሚዳርጋቸው ተነግሯቸዋል (ዘኁ 33:55, 56፤ w08 2/15 27 አን. 5-6፤ it-1 404 አን. 2)
ይሖዋን ማስደሰት ከፈለግን በሥነ ምግባርም ሆነ በመንፈሳዊ እንድንበከል የሚያደርጉ ልማዶችን ሙሉ በሙሉ ማስወገድ አለብን። (ያዕ 1:21) ይሖዋ፣ የኃጢአት ዝንባሌያችንን እንድንዋጋና በካይ የሆነውን የዓለም ተጽዕኖ እንድንቋቋም ኃይል ይሰጠናል።