ክርስቲያናዊ ሕይወት
“ፍቅር . . . ሁሉን ተስፋ ያደርጋል”
ከራስ ወዳድነት ነፃ የሆነ ፍቅር ወንድሞቻችን ጥሩ ውሳኔ እንደሚያደርጉ ተስፋ እንድናደርግ ያነሳሳናል። (1ቆሮ 13:4, 7) ለምሳሌ አንድ ወንድም ኃጢአት ሠርቶ ተግሣጽ ቢሰጠው እሱን ለመርዳት ለሚደረገው ጥረት በጎ ምላሽ እንደሚሰጥ ተስፋ እናደርጋለን። ደካማ እምነት ያላቸውን ሰዎች በትዕግሥት እንይዛቸዋለን፤ እንዲሁም እነሱን ለመርዳት ጥረት እናደርጋለን። (ሮም 15:1) አንድ ሰው ጉባኤውን ቢተው ደግሞ አንድ ቀን እንደሚመለስ ተስፋ እናደርጋለን።—ሉቃስ 15:17, 18
ፍቅር የሚያደርጋቸውና የማያደርጋቸው ነገሮች—ሁሉን ተስፋ ያደርጋል የሚለውን ቪዲዮ ተመልከት፤ ከዚያም የሚከተሉትን ጥያቄዎች ለመመለስ ሞክር፦
-
አበኔር ምን ዓይነት ለውጥ አደረገ?
-
ዳዊት ለአበኔር ጥያቄ ምን ምላሽ ሰጠ? ኢዮዓብስ?
-
ወንድሞቻችን ጥሩ ውሳኔ እንደሚያደርጉ ተስፋ ማድረግ ያለብን ለምንድን ነው?