ክርስቲያናዊ ሕይወት
“ፍቅር በዓመፅ አይደሰትም”
እውነተኛ ክርስቲያኖች በሁሉም የሕይወታቸው ዘርፎች ፍቅር ለማሳየት ጥረት ያደርጋሉ። “ፍቅር በዓመፅ አይደሰትም።” (1ቆሮ 13:4, 6) በመሆኑም እንደ ፆታ ብልግና እና ዓመፅ ያሉትን ነገሮች ከሚያበረታቱ መዝናኛዎች እንርቃለን። በተጨማሪም ጉዳት ያደረሱብንን ሰዎች ጨምሮ በሌሎች ላይ መጥፎ ነገር ሲደርስ አንደሰትም።—ምሳሌ 17:5
ፍቅር የሚያደርጋቸውና የማያደርጋቸው ነገሮች—በዓመፅ አይደሰትም የሚለውን ቪዲዮ ተመልከት፤ ከዚያም የሚከተሉትን ጥያቄዎች ለመመለስ ሞክር፦
-
ዳዊት ሳኦልና ዮናታን እንደሞቱ ሲነገረው ምን ተሰማው?
-
ዳዊት ለሳኦልና ለዮናታን የትኛውን ሙሾ አቀናበረ?
-
ዳዊት በሳኦል ሞት ያልተደሰተው ለምንድን ነው?