በቀጥታ ወደ ዋናው ጉዳይ ግባ

በቀጥታ ወደ ርዕስ ማውጫው ሂድ

ክርስቲያናዊ ሕይወት

ለኢኮኖሚ ቀውስ ተዘጋጅታችኋል?

ለኢኮኖሚ ቀውስ ተዘጋጅታችኋል?

በዓለም ዙሪያ የኢኮኖሚ አለመረጋጋት ቢከሰት አንደናገጥም። ለምን? ምክንያቱም የምንኖረው በመጨረሻዎቹ ቀናት መጨረሻ እንደሆነ እናውቃለን፤ መጽሐፍ ቅዱስም ተስፋችንን “አስተማማኝነት በሌለው ሀብት” ላይ እንዳንጥል ይመክረናል። (1ጢሞ 6:17፤ 2ጢሞ 3:1) ለኢኮኖሚ ቀውስ መዘጋጀት የምንችልበትን መንገድ በተመለከተ ከኢዮሳፍጥ ምሳሌ ምን እንማራለን?

የጠላት ሠራዊት ይሁዳን ለመውረር በመጣበት ወቅት ኢዮሳፍጥ በይሖዋ ታምኗል። (2ዜና 20:9-12) በተጨማሪም ምሽጎችን በመገንባትና የጦር ሰፈሮችን በማቋቋም ብሔሩን ለሚሰነዘርባቸው ጥቃት ለማዘጋጀት ተግባራዊ እርምጃ ወስዷል። (2ዜና 17:1, 2, 12, 13) እኛም የሚያጋጥመንን አስቸጋሪ ሁኔታ ለመቋቋም እንደ ኢዮሳፍጥ በይሖዋ መታመንና ተግባራዊ እርምጃ መውሰድ ይኖርብናል።

አደጋ ቢያጋጥም ዝግጁ ናችሁ? የሚለውን ቪዲዮ ተመልከት፤ ከዚያም የሚከተሉትን ጥያቄዎች ለመመለስ ሞክር፦

  • ለአደጋ ለመዘጋጀት በግለሰብ ደረጃ ምን ማድረግ እንችላለን?

  • ሌሎችን ለመርዳት መዘጋጀት የምንችለው እንዴት ነው?