በቀጥታ ወደ ዋናው ጉዳይ ግባ

ከግራ ወደ ቀኝ፦ ወንድም አንቶን ቼርምኒክ፣ ወንድም ሰርጌ ኮሮልቹክ እና ወንድም ዲሚትሪ ቲሽቼንኮ

ሐምሌ 14, 2021| የታደሰው፦ ታኅሣሥ 2, 2022
ሩሲያ

ወቅታዊ መረጃ—ብይን ተላለፈ | ሦስት ወንድሞች ለስደት መዘጋጀታቸው ታማኝነታቸውን እንዲጠብቁ ረድቷቸዋል

ወቅታዊ መረጃ—ብይን ተላለፈ | ሦስት ወንድሞች ለስደት መዘጋጀታቸው ታማኝነታቸውን እንዲጠብቁ ረድቷቸዋል

ኅዳር 30, 2022 በፕሪሞርይስ ክልል የሚገኘው የኡሱሪስኪ አውራጃ ፍርድ ቤት በወንድም አንቶን ቼርምኒክ፣ በወንድም ሰርጌ ኮሮልቹክ እና በወንድም ዲሚትሪ ቲሽቼንኮ ላይ የጥፋተኝነት ብይን አስተላልፏል። ሦስቱም የስድስት ዓመት የገደብ እስራት ተላልፎባቸዋል። በእርግጥ አሁን ወህኒ አይወርዱም።

የክሱ ሂደት

  1. መስከረም 23, 2020

    የአንቶን፣ የሰርጌና የዲሚትሪ ጉዳይ በፍርድ ቤት መታየት ጀመረ

  2. ሐምሌ 7, 2020

    አንቶን፣ ሰርጌ እና ዲሚትሪ “ጽንፈኛ” በሆነ እና እገዳ በተጣለበት ሃይማኖታዊ ድርጅት ውስጥ የአመራር ቦታ አላቸው የሚል ክስ ተመሠረተባቸው

  3. ሰኔ 18, 2019

    ሰርጌ ለሁለት ቀን ያህል በማረፊያ ቤት እንዲቆይ ተደረገ

አጭር መግለጫ

በአንቶን፣ በሰርጌና በዲሚትሪ ላይ የሚደርሰው ፈተናና ስደት ቢቀጥልም ይሖዋ ለታማኝነታቸው እንደሚባርካቸው እርግጠኞች ነን።—ምሳሌ 28:20