በቀጥታ ወደ ዋናው ጉዳይ ግባ

ከግራ ወደ ቀኝ፦ ወንድም ማራት አብዱልጋሊሞቭ፣ ወንድም አርሴን አብዱላዬቭ፣ ወንድም አንቶን ዴርጋሌቭ እና እህት ማሪያ ካርፖቫ

ነሐሴ 20, 2021 | የታደሰው፦ ኅዳር 28, 2022
ሩሲያ

ወቅታዊ መረጃ—ብይን ተላለፈ | በዳግስታን የሚኖሩ ሦስት ወንድሞችና አንዲት እህት በማረፊያ ቤት ሳሉ ይሖዋ ደግፏቸዋል

ወቅታዊ መረጃ—ብይን ተላለፈ | በዳግስታን የሚኖሩ ሦስት ወንድሞችና አንዲት እህት በማረፊያ ቤት ሳሉ ይሖዋ ደግፏቸዋል

ኅዳር 24, 2022 በዳግስታን ሪፑብሊክ፣ በማሃችካላ የሚገኘው የኪሮቭስኪ አውራጃ ፍርድ ቤት በወንድም ማራት አብዱልጋሊሞቭ፣ በወንድም አርሴን አብዱላዬቭ፣ በወንድም አንቶን ዴርጋሌቭ እና በእህት ማሪያ ካርፖቫ ላይ የጥፋተኝነት ብይን አስተላልፏል። ከስድስት ዓመት እስከ ስድስት ዓመት ተኩል የሚደርስ የገደብ እስራት ተፈርዶባቸዋል። በእርግጥ በአሁኑ ወቅት ወህኒ አይወርዱም።

የክሱ ሂደት

  1. ግንቦት 27, 2020

    ማራት፣ አርሴን፣ አንቶን እና ማሪያ ለ362 ቀናት በማረፊያ ቤት ከቆዩ በኋላ ወደ ቁም እስር ተዛወሩ

  2. ሰኔ 4, 2019

    በማሃችካላ የሚገኘው የሶቬትስኪ አውራጃ ፍርድ ቤት አራቱም ማረፊያ ቤት እንዲቆዩ አዘዘ

  3. ሰኔ 1, 2019

    የሩሲያ የደህንነት አባላት (የሩሲያ የሚስጥር ፖሊስ) በዳግስታን የሚኖሩ 13 የይሖዋ ምሥክሮችን ቤቶች ፈተሹ

  4. ግንቦት 27, 2019

    በዳግስታን የሚገኘው የሩሲያ የደህንነት ቢሮ በማራት፣ በአርሴን፣ በአንቶን እና በማሪያ ላይ የወንጀል ክስ መሠረተ

አጭር መግለጫ

ይሖዋ አምላክ ምንጊዜም ልክ እንደ ስሙ ሕዝቦቹን ለመጠበቅና ለመደገፍ መሆን የሚያስፈልገውን ሁሉ እንደሚሆን ሙሉ በሙሉ እንተማመናለን።—ዘፀአት 3:14

ፍርድ ቤቱ ብይን የሚያስተላልፍበትን ቀን አስቀድሞ የማያሳውቅበት ጊዜ አለ።