በቀጥታ ወደ ዋናው ጉዳይ ግባ

ከግራ ወደ ቀኝ፣ ከላይ፦ ወንድም ቭላዲሚር ኮችኔቭ እና ባለቤቱ ገሊና፣ ወንድም ቭላዲስላቭ ኮልባኖቭ። ከታች፦ ወንድም ፓቬል ሌኮንትሴቭ እና ባለቤቱ ኦክሳና፣ ወንድም ሰርጌ ሎጉኖቭ እና ባለቤቱ ላሪሳ፣ ወንድም ኒኮላይ ዡጊን እና ባለቤቱ ገሊና

ጥቅምት 1, 2021 | የታደሰው፦ ነሐሴ 29, 2023
ሩሲያ

ወቅታዊ መረጃ—ወንድሞች ተፈረደባቸው | አምስት ወንድሞች ስደት ቢደርስባቸውም ለመጽናት ቆርጠዋል

ወቅታዊ መረጃ—ወንድሞች ተፈረደባቸው | አምስት ወንድሞች ስደት ቢደርስባቸውም ለመጽናት ቆርጠዋል

ነሐሴ 28, 2023 በኦረንበርግ የሚገኘው የፕሮሚሽሌኒ አውራጃ ፍርድ ቤት፣ በወንድም ቭላዲሚር ኮችኔቭ፣ በወንድም ቭላዲስላቭ ኮልባኖቭ፣ በወንድም ፓቬል ሌኮንትሴቭ፣ በወንድም ሰርጌ ሎጉኖቭ እና በወንድም ኒኮላይ ዡጊን ላይ የጥፋተኝነት ብይን አስተላልፏል። ወንድሞች ከሁለት ዓመት ተኩል እስከ ሦስት ዓመት ተኩል የሚደርስ የገደብ እስራት ተፈርዶባቸዋል። በአሁኑ ወቅት ወህኒ አይወርዱም።

የክሱ ሂደት

  1. መጋቢት 1, 2021

    ክሱ ወደ አቃቤ ሕግ ቢሮ ከተመለሰ ከአንድ ዓመት በላይ ካለፈ በኋላ ጉዳያቸው በኦረንበርግ በሚገኘው ፕሮሚሽሌኒ አውራጃ ፍርድ ቤት መታየት ጀመረ

  2. ጥር 14, 2020

    ክሱ በግልጽ ባለመቀመጡ የተነሳ ወደ አቃቤ ሕግ ቢሮ ተመለሰ

  3. ነሐሴ 3, 2018

    ቭላዲሚር በማረፊያ ቤት 79 ቀናት ካሳለፈ በኋላ በቁም እስር እንዲቆይ ተደረገ

  4. ግንቦት 16, 2018

    ባለሥልጣናቱ በኦረንበርግ ክልል የሚኖሩ 19 ቤተሰቦችን ቤት ፈተሹ። ቭላዲሚርን እና ቭላዲስላቭን ማረፊያ ቤት አስገቧቸው። ከሦስት ቀናት በኋላ ቭላዲስላቭ ከማረፊያ ቤት ተለቆ በቁም እስር እንዲቆይ ተደረገ

  5. ግንቦት 14, 2018

    በኦረንበርግ ክልል የሚገኘው የሩሲያ ፌዴሬሽን የምርመራ ኮሚቴ በአምስቱም ወንድሞች ላይ ክስ መሠረተ

አጭር መግለጫ

ወንድሞቻችን በእምነታቸው ምክንያት ክስ ከተመሠረተባቸው ከሦስት ዓመት የሚበልጥ ጊዜ ቢያልፍም እነዚህ ወንድሞች ለይሖዋ ታማኝ ሆነው ለመቀጠል እንደቆረጡ ምንም አያሻማም። ይሖዋም ለእነሱ ታማኝ እንደሆነ በግልጽ ማየት ይቻላል።—2 ሳሙኤል 22:26