በቀጥታ ወደ ዋናው ጉዳይ ግባ

ወንድም ዬቭጌኒ ቢቱሶቭ እና ሊዮኒድ ድሩዢኒን

ኅዳር 30, 2022 | የታደሰው፦ ታኅሣሥ 29, 2022
ሩሲያ

ወቅታዊ መረጃ—ወንድሞች ታሰሩ | ክርስቲያናዊ ባሕርያትን እንዲያዳብሩ ረድቷቸዋል

ወቅታዊ መረጃ—ወንድሞች ታሰሩ | ክርስቲያናዊ ባሕርያትን እንዲያዳብሩ ረድቷቸዋል

በአሙር ክልል የሚገኘው የዜይስኪ አውራጃ ፍርድ ቤት፣ በወንድም ዬቭጌኒ ቢቱሶቭ እና በወንድም ሊዮኒድ ድሩዢኒን ላይ የጥፋተኝነት ብይን አስተላልፏል። ወንድም ቢቱሶቭ የስድስት ዓመት፣ ወንድም ድሩዢኒን ደግሞ የስድስት ዓመት ተኩል እስራት ተፈርዶባቸዋል። ብይኑ እንደተላለፈ ከፍርድ ቤት ወደ ወህኒ ወርደዋል።

አጭር መግለጫ

ስለ ወንድሞቻችንና እህቶቻችን ስናስብ ኩራት ይሰማናል፤ ምክንያቱም በጽናትና በትዕግሥት ብቁ የአምላክ አገልጋዮች መሆናቸውን እያስመሠከሩ ነው።—2 ቆሮንቶስ 6:3-10

የክሱ ሂደት

  1. መጋቢት 21, 2019

    የሕግ አስከባሪ አካላት፣ ዜያ ውስጥ የሚገኙ በርካታ የይሖዋ ምሥክሮችን ቤቶች ፈተሹ፤ የዬቭጌኒና የሊዮኒድ ቤትም ተፈተሸ

  2. ነሐሴ 10, 2020

    የወንጀል ክስ ተመሠረተባቸው

  3. ጥቅምት 13, 2020

    የሕግ አስከባሪ አካላት፣ የዬቭጌኒንና የሊዮኒድን ቤት ድጋሚ ፈተሹ። ሊዮኒድ ወደ ጣቢያ ተወስዶ ለሁለት ሰዓት ምርመራ ተደረገበት

  4. ሰኔ 20, 2022

    ክሳቸው በፍርድ ቤት መታየት ጀመረ