በቀጥታ ወደ ዋናው ጉዳይ ግባ

ከግራ ወደ ቀኝ፦ ወንድም ቭላድሚር ሜልኒክ፣ ወንድም ቭላድሚር ፒስካሬቭ እና ወንድም አርተር ፑቲንሴቭ

ግንቦት 20, 2022 | የታደሰው፦ ጥቅምት 17, 2023
ሩሲያ

ወቅታዊ መረጃ—ወንድሞች እስር ተፈረደባቸው | ቤተሰቦች በይሖዋ እገዛ ስደትን በጽናት እየተቋቋሙ ነው

ወቅታዊ መረጃ—ወንድሞች እስር ተፈረደባቸው | ቤተሰቦች በይሖዋ እገዛ ስደትን በጽናት እየተቋቋሙ ነው

ጥቅምት 13, 2023 በኦርዮል ከተማ የሚገኘው የሶቪየትስኪ አውራጃ ፍርድ ቤት ወንድም ቭላድሚር ሜልኒክ፣ ወንድም ቭላድሚር ፒስካሬቭ እና ወንድም አርተር ፑቲንሴቭ ጥፋተኞች ናቸው በማለት በእያንዳንዳቸው ላይ የስድስት ዓመት እስራት ፍርድ አስተላልፏል። ሦስቱም ወንድሞች ከታኅሣሥ 2020 ጀምሮ ማረፊያ ቤት የነበሩ ሲሆን አሁንም ወህኒ ይቆያሉ።

የክሱ ሂደት

  1. ታኅሣሥ 8, 2020

    በወንድም ሜልኒክ፣ በወንድም ፒስካሬቭ እና በወንድም ፑቲንሴቭ ላይ ክስ ተመሠረተ

  2. ታኅሣሥ 9, 2020

    ፖሊሶች በኦርዮል የሚገኙ ስምንት የይሖዋ ምሥክሮችን ቤቶች ፈተሹ፤ ከእነዚህ መካከል የሦስቱ ወንድሞች ቤቶች ይገኙበታል። በኋላም ወደ ጣቢያ ተወሰዱ

  3. ታኅሣሥ 11, 2020

    ወንድም ሜልኒክ እና ወንድም ፒስካሬቭ ማረፊያ ቤት እንዲገቡ ተደረገ

  4. ታኅሣሥ 14, 2020

    ወንድም ፑቲንሴቭ ማረፊያ ቤት እንዲገባ ተደረገ

  5. ጥር 19, 2021

    ወንድም ፒስካሬቭ አስቸኳይ ክትትል የሚፈልጉ የጤና እክሎች እንዳሉበት ለባለሥልጣናቱ ተነገራቸው፤ ሆኖም አስፈላጊውን ሕክምናም ሆነ መድኃኒት እንዳያገኝ ከለከሉት

  6. ጥር 21, 2021

    ወንድም ፒስካሬቭ ባለቤቱ ያመጣችለትን መድኃኒት እንዲቀበል ተፈቀደለት፤ የሕክምና ክትትል ለማድረግ ግን አልተፈቀደለትም

  7. ሰኔ 24, 2021

    ወንድም ፒስካሬቭ ለምርመራ ወደ ሆስፒታል ተወሰደ፤ ስትሮክ እንዳጋጠመው ታወቀ። ይህ የጤና ችግር እንዳጋጠመው እየታወቀም ወደ ማረፊያ ቤት እንዲመለስ ተደረገ

  8. ጥቅምት 29, 2021

    ወንድሞች ‘ጽንፈኛ ተብሎ የተፈረጀን ድርጅት እንቅስቃሴዎች አስተባብረዋል’ የሚል ክስ ተመሠረተባቸው

  9. ጥር 31, 2022

    ጉዳያቸው በፍርድ ቤት መታየት ጀመረ

አጭር መግለጫ

እነዚህ ቤተሰቦች ለጊዜው መለያየት ግድ ሆኖባቸዋል፤ ከይሖዋ ፍቅራዊ እንክብካቤና ጥበቃ ሊለያቸው የሚችል አንዳች ነገር እንደሌለ ማወቃችን ግን ያጽናናናል።—ሮም 8:38, 39

a b c ይህ ዜና በተጠናቀረበት ወቅት ወንድም ሜልኒክ፣ ወንድም ፒስካሬቭ እና ወንድም ፑቲንሴቭ ማረፊያ ቤት ስለነበሩ የእነሱን አስተያየት ማግኘት አልተቻለም።