በቀጥታ ወደ ዋናው ጉዳይ ግባ

ከግራ ወደ ቀኝ፦ ወንድም ቭላድሚር ማላዲካ፣ ወንድም ቭላድሚር ሳካዳና ባለቤቱ ስቬትላና እንዲሁም ወንድም ዬቭጌኒ ዡኮቭ

ግንቦት 9, 2022
ዓለም አቀፋዊ ዜና

ወቅታዊ መረጃ—ወንድሞች ታሰሩ | በክራይሚያ ያሉ ቤተሰቦች በይሖዋ እርዳታ ጸንተዋል

ወቅታዊ መረጃ—ወንድሞች ታሰሩ | በክራይሚያ ያሉ ቤተሰቦች በይሖዋ እርዳታ ጸንተዋል

ጥቅምት 6, 2022 በሴቫስቶፖል የሚገኘው የናኪሞቭስኪ አውራጃ ፍርድ ቤት በወንድም ቭላድሚር ማላዲካ፣ በወንድም ቭላድሚር ሳካዳ እና በወንድም ዬቭጌኒ ዡኮቭ ላይ ብይን አስተላልፏል። እያንዳንዳቸው የስድስት ዓመት እስራት ተፈርዶባቸዋል። ወዲያውኑ ወህኒ ወርደዋል።

የክሱ ሂደት

  1. ጥቅምት 1, 2020

    የፊዴራል ደህንነት አባላት የወንድም ማላዲካ የወንድም ሳካዳ እና የወንድም ዡኮቭ ቤት ጨምሮ በሴቫስቶፖል የሚኖሩ ዘጠኝ የይሖዋ ምሥክር ቤተሰቦችን ቤቶች ፈተሹ። የወንድም ማላዲካ ቤት በተፈተሸበት ወቅት ፖሊሶቹ በአንድ ትንሽ ዕቃ ውስጥ ዱቄት ወተት አገኙ። ፖሊሶቹ ዱቄቱ “አደንዛዥ ዕፅ” እንደሚመስል በመናገር ወንድም ማላዲካን እና ባለቤቱን ናታሊያን ለምርመራ ወደ አእምሮ ሐኪም ቤት ላኳቸው። ናታሊያ በዚያው ዕለት ተለቀቀች። ወንድም ማላዲካ እንዲሁም ወንድም ሳካዳ እና ወንድም ዡኮቭ ግን ወደ ጊዜያዊ ማቆያ ተወሰዱ። በቀጣዩ ቀን ወደ ማረፊያ ቤት ተላኩ

  2. መጋቢት 23, 2021

    ወንድም ሳካዳ ከማረፊያ ቤት ተለቆ በቁም እስር እንዲቆይ ተደረገ። የእንቅስቃሴ መቆጣጠሪያ መሣሪያ እንዲያደርግ የተገደደ ከመሆኑም ሌላ ኢንተርኔት እንዳይጠቀም፣ ስልክ እንዳይደውል እንዲሁም በክሱ ውስጥ ከተካተቱት ሌሎች ወንድሞች ጋር እንዳይነጋገር ተከለከለ

  3. መጋቢት 30, 2021

    ወንድም ማላዲካ ከማረፊያ ቤት ተለቆ በቁም እስር እንዲቆይ ተደረገ

  4. ግንቦት 17, 2021

    ወንድም ዡኮቭ ከሰባት ወር በላይ በማረፊያ ቤት ከቆየ በኋላ ተለቆ በቁም እስር እንዲቆይ ተደረገ

  5. መስከረም 30, 2021

    ጉዳያቸው በፍርድ ቤት መታየት ጀመረ

አጭር መግለጫ

ይሖዋ እነዚህን ወንድሞች ጨምሮ በክራይሚያ ስደት እየደረሰባቸው ያሉትን ሁሉ ልባቸውን እንደሚያጸናላቸው እርግጠኞች ነን።—1 ተሰሎንቄ 3:12, 13