መዝሙር 118:1-29

  • ይሖዋ ላስገኘው ድል ምስጋና ማቅረብ

    • ‘ያህን ተጣራሁ፤ እሱም መለሰልኝ’ (5)

    • “ይሖዋ ከጎኔ ነው” (6, 7)

    • የተናቀው ድንጋይ የማዕዘን ራስ ድንጋይ ይሆናል (22)

    • “በይሖዋ ስም የሚመጣው” (26)

118  ይሖዋ ጥሩ+ ስለሆነ ምስጋና አቅርቡለት፤ታማኝ ፍቅሩ ለዘላለም ጸንቶ ይኖራል።   እስራኤል እንዲህ ይበል፦ “ታማኝ ፍቅሩ ለዘላለም ጸንቶ ይኖራል።”   ከአሮን ቤት የሆኑ እንዲህ ይበሉ፦ “ታማኝ ፍቅሩ ለዘላለም ጸንቶ ይኖራል።”   ይሖዋን የሚፈሩ እንዲህ ይበሉ፦ “ታማኝ ፍቅሩ ለዘላለም ጸንቶ ይኖራል።”   በተጨነቅኩ ጊዜ ያህን* ተጣራሁ፤ያህም መለሰልኝ፤ ደህንነት ወደማገኝበት ስፍራም* አመጣኝ።+   ይሖዋ ከጎኔ ነው፤ አልፈራም።+ ሰው ምን ሊያደርገኝ ይችላል?+   ይሖዋ ረዳቴ ሆኖ* ከጎኔ አለ፤+የሚጠሉኝን ሰዎች በድል አድራጊነት እመለከታለሁ።+   በሰው ከመታመን ይልቅ፣ይሖዋን መጠጊያ ማድረግ ይሻላል።+   በመኳንንት ከመታመን ይልቅ፣ይሖዋን መጠጊያ ማድረግ ይሻላል።+ 10  ብሔራት ሁሉ ከበቡኝ፤እኔ ግን በይሖዋ ስምመከትኳቸው።+ 11  ከበቡኝ፤ አዎ፣ ዙሪያዬን ከበቡኝ፤እኔ ግን በይሖዋ ስምመከትኳቸው። 12  እንደ ንብ ከበቡኝ፤ሆኖም በእሳት እንደተያያዘ ቁጥቋጦ ወዲያውኑ ጠፉ። እኔም በይሖዋ ስምመከትኳቸው።+ 13  እወድቅ ዘንድ በኃይል ተገፋሁ፤*ይሖዋ ግን ረዳኝ። 14  ያህ መጠለያዬና ብርታቴ ነው፤አዳኝም ሆኖልኛል።+ 15  በጻድቃን ድንኳኖች ውስጥ፣የሐሴትና የመዳን* ድምፅ ይሰማል። የይሖዋ ቀኝ እጅ ኃይሉን ያሳያል።+ 16  የይሖዋ ቀኝ እጅ ከፍ ከፍ አለ፤የይሖዋ ቀኝ እጅ ኃይሉን ያሳያል።+ 17  የያህን ሥራዎች አስታውቅ ዘንድበሕይወት እኖራለሁ እንጂ አልሞትም።+ 18  ያህ ጠንከር ያለ ተግሣጽ ሰጥቶኛል፤+ሆኖም ለሞት አሳልፎ አልሰጠኝም።+ 19  የጽድቅን በሮች ክፈቱልኝ፤+በዚያ ገብቼ ያህን አወድሳለሁ። 20  ይህ የይሖዋ በር ነው። ጻድቃን በዚያ በኩል ይገባሉ።+ 21  መልስ ስለሰጠኸኝናአዳኝ ስለሆንከኝ አወድስሃለሁ።+ 22  ግንበኞች የናቁት ድንጋይየማዕዘን ራስ ድንጋይ* ሆነ።+ 23  ይህ የይሖዋ ሥራ ነው፤+ለዓይናችንም ድንቅ ነው።+ 24  ይህ ይሖዋ የሠራው ቀን ነው፤በዚህ ቀን እንደሰታለን፤ ሐሴትም እናደርጋለን። 25  ይሖዋ ሆይ፣ እባክህ እንድታድነን እንለምንሃለን! ይሖዋ ሆይ፣ እባክህ ድል አቀዳጀን! 26  በይሖዋ ስም የሚመጣው የተባረከ ነው፤+በይሖዋ ቤት ሆነን እንባርካችኋለን። 27  ይሖዋ አምላክ ነው፤ብርሃን ይሰጠናል።+ ቅርንጫፎች በመያዝ ወደ በዓሉ ከሚጓዙት ጋር ተቀላቅላችሁ+እስከ መሠዊያው ቀንዶች+ ድረስ ሂዱ። 28  አንተ አምላኬ ነህ፤ እኔም አወድስሃለሁ፤አምላኬ ሆይ፣ ከፍ ከፍ አደርግሃለሁ።+ 29  ይሖዋ ጥሩ ስለሆነ ምስጋና አቅርቡለት፤+ታማኝ ፍቅሩ ለዘላለም ጸንቶ ይኖራል።+

የግርጌ ማስታወሻ

“ያህ” የይሖዋ ስም አጭር መጠሪያ ነው።
ወይም “ሰፊ ወደሆነ ስፍራም።”
“ከሚረዱኝ ሰዎች ጋር” ማለትም ሊሆን ይችላል።
“በኃይል ገፋኸኝ” ማለትም ሊሆን ይችላል።
ወይም “የድል።”
ቃል በቃል “የማዕዘኑ ራስ።”