መዝሙር 124:1-8

  • “ይሖዋ ከእኛ ጋር ባይሆን ኖሮ”

    • ከተሰበረ ወጥመድ ማምለጥ (7)

    • “የይሖዋ ስም ረዳታችን ነው” (8)

ወደ ላይ የመውጣት መዝሙር። የዳዊት መዝሙር። 124  “ይሖዋ ከእኛ ጋር ባይሆን ኖሮ፣”+ እስራኤል እንዲህ ይበል፦   “ይሖዋ ከእኛ ጋር ባይሆን ኖሮ፣+ሰዎች እኛን ለማጥቃት በተነሱ ጊዜ፣+   ቁጣቸው በእኛ ላይ በነደደ ጊዜ፣+በሕይወት ሳለን በዋጡን ነበር።+   በዚያን ጊዜ ውኃ ጠራርጎ በወሰደን፣ጎርፍም ባጥለቀለቀን ነበር።*+   ኃይለኛ ውኃ በዋጠን ነበር።*   ለጥርሳቸው ሲሳይ እንድንሆን አሳልፎ ስላልሰጠንይሖዋ ይወደስ።   ከአዳኝ ወጥመድእንዳመለጠች ወፍ ነን፤*+ወጥመዱ ተሰበረ፤እኛም አመለጥን።+   ሰማይንና ምድርን የሠራውየይሖዋ ስም ረዳታችን ነው።”+

የግርጌ ማስታወሻ

ወይም “ነፍሳችንን ጎርፍ ባጥለቀለቃት ነበር።”
ወይም “ነፍሳችንን በዋጣት ነበር።”
ወይም “ነፍሳችን ከአዳኝ ወጥመድ እንዳመለጠች ወፍ ነች።”