መዝሙር 26:1-12
የዳዊት መዝሙር።
26 ይሖዋ ሆይ፣ በንጹሕ አቋም* ተመላልሻለሁና ፍረድልኝ፤+ያለምንም ማወላወል በይሖዋ ታምኛለሁ።+
2 ይሖዋ ሆይ፣ መርምረኝ፤ ፈትነኝም፤በውስጤ ያለውን ሐሳብና* ልቤን አጥራልኝ።+
3 ታማኝ ፍቅርህ ምንጊዜም በፊቴ ነውና፤በእውነትህም እመላለሳለሁ።+
4 አታላይ ከሆኑ ሰዎች ጋር አልቀራረብም፤*+ማንነታቸውን ከሚደብቁም እርቃለሁ።*
5 ከክፉ ሰዎች ጋር መሆን እጠላለሁ፤+ከክፉዎችም ጋር መቀራረብ* አልፈልግም።+
6 ንጹሕ መሆኔን ለማሳየት እጆቼን እታጠባለሁ፤ይሖዋ ሆይ፣ መሠዊያህን እዞራለሁ፤
7 ይህም የምስጋናን ድምፅ አሰማ ዘንድ፣+ድንቅ ሥራዎችህንም ሁሉ አውጅ ዘንድ ነው።
8 ይሖዋ ሆይ፣ የምትኖርበትን ቤት፣+የክብርህንም ማደሪያ ቦታ እወዳለሁ።+
9 ከኃጢአተኞች ጋር አታጥፋኝ፤*+ሕይወቴንም ከዓመፀኞች* ጋር አታስወግድ፤
10 እጆቻቸው አሳፋሪ ድርጊት ይፈጽማሉ፤ቀኝ እጃቸውም በጉቦ የተሞላ ነው።
11 እኔ ግን ንጹሕ አቋሜን ጠብቄ እመላለሳለሁ።
ታደገኝ፤* ሞገስም አሳየኝ።
12 እግሬ በደልዳላ ስፍራ ቆሟል፤+በታላቅ ጉባኤ መካከል* ይሖዋን አወድሳለሁ።+