መዝሙር 79:1-13

  • ብሔራት የአምላክን ሕዝብ በወረሩ ጊዜ የቀረበ ጸሎት

    • “መሳለቂያ ሆንን” (4)

    • ‘ለስምህ ስትል እርዳን’ (9)

    • ‘ጎረቤቶቻችንን ሰባት እጥፍ አድርገህ ብድራታቸውን ክፈላቸው’ (12)

የአሳፍ+ ማህሌት። 79  አምላክ ሆይ፣ ብሔራት ርስትህን+ ወረውታል፤ቅዱስ መቅደስህንም አርክሰዋል፤+ኢየሩሳሌምን የፍርስራሽ ክምር አድርገዋታል።+   የአገልጋዮችህን ሬሳ ለሰማይ ወፎች፣የታማኝ አገልጋዮችህንም ሥጋ ለምድር አራዊት ምግብ አድርገው ሰጥተዋል።+   ደማቸውን በኢየሩሳሌም ዙሪያ እንደ ውኃ አፈሰሱ፤እነሱንም የሚቀብር አንድም ሰው አልተረፈም።+   በጎረቤቶቻችን ዘንድ መሳለቂያ ሆንን፤+በዙሪያችን ያሉትም ያፌዙብናል፤ ደግሞም ይዘብቱብናል።   ይሖዋ ሆይ፣ የምትቆጣው እስከ መቼ ነው? ለዘላለም?+ ቁጣህስ እንደ እሳት የሚነደው እስከ መቼ ነው?+   አንተን በማያውቁ ብሔራት፣ስምህንም በማይጠሩ መንግሥታት ላይ ቁጣህን አፍስስ።+   ያዕቆብን በልተውታልና፤የትውልድ አገሩንም አውድመዋል።+   አባቶቻችን በሠሩት ስህተት እኛን ተጠያቂ አታድርገን።+ ፈጥነህ ምሕረት አድርግልን፤+በጭንቀት ተውጠናልና።   አዳኛችን የሆንክ አምላክ ሆይ፣ለታላቁ ስምህ ስትል እርዳን፤+ለስምህም ስትል ታደገን፤ ኃጢአታችንንም ይቅር በለን።*+ 10  ብሔራት “አምላካቸው የት አለ?” ለምን ይበሉ?+ በፈሰሰው የአገልጋዮችህ ደም የተነሳ የሚወሰድባቸውን የበቀል እርምጃ፣ዓይናችን እያየ ብሔራት ይወቁት።+ 11  እስረኛው የሚያሰማውን ሲቃ ስማ።+ ሞት የተፈረደባቸውን* በታላቅ ኃይልህ* አድናቸው።*+ 12  ይሖዋ ሆይ፣ ጎረቤቶቻችን በአንተ ላይ በመሳለቃቸው+ሰባት እጥፍ አድርገህ ብድራታቸውን ክፈላቸው።+ 13  በዚህ ጊዜ እኛ ሕዝቦችህ፣ በመስክህ ያሰማራኸን መንጋ፣+ለዘላለም ምስጋና እናቀርብልሃለን፤ከትውልድ እስከ ትውልድም ውዳሴህን እናሰማለን።+

የግርጌ ማስታወሻ

ቃል በቃል “ሸፍንልን።”
ቃል በቃል “የሞት ወንዶች ልጆችን።”
ቃል በቃል “ክንድህ።”
“ነፃ አውጣቸው” ማለትም ሊሆን ይችላል።