መዝሙር 86:1-17

  • እንደ ይሖዋ ያለ አምላክ የለም

    • ይሖዋ ይቅር ለማለት ዝግጁ ነው (5)

    • ብሔራት ሁሉ አምላክን ያመልካሉ (9)

    • “መንገድህን አስተምረኝ” (11)

    • “ልቤን አንድ አድርግልኝ” (11)

የዳዊት ጸሎት። 86  ይሖዋ ሆይ፣ ጆሮህን ወደ እኔ አዘንብል፤* ደግሞም መልስልኝ፤ጎስቋላና ድሃ ነኝና።+   እኔ ታማኝ ስለሆንኩ ሕይወቴን* ጠብቃት።+ በአንተ የሚታመነውን አገልጋይህን አድነው፤አንተ አምላኬ ነህና።+   ይሖዋ ሆይ፣ ሞገስ አሳየኝ፤+ቀኑን ሙሉ አንተን እጣራለሁና።+   አገልጋይህን ደስ አሰኘው፤*ይሖዋ ሆይ፣ የአንተን እርዳታ እሻለሁና።*   ይሖዋ ሆይ፣ አንተ ጥሩ ነህና፤+ ይቅር ለማለትም ዝግጁ ነህ፤+አንተን ለሚጠሩ ሁሉ የምታሳየው ታማኝ ፍቅር ወሰን የለውም።+   ይሖዋ ሆይ፣ ጸሎቴን አዳምጥ፤እርዳታ ለማግኘት የማቀርበውንም ልመና በትኩረት ስማ።+   አንተ መልስ ስለምትሰጠኝ፣+በተጨነቅኩ ቀን አንተን እጣራለሁ።+   ይሖዋ ሆይ፣ ከአማልክት መካከል እንደ አንተ ያለ የለም፤+ከአንተ ሥራ ጋር የሚወዳደር አንድም ሥራ የለም።+   ይሖዋ ሆይ፣ አንተ የሠራሃቸው ብሔራት ሁሉ ይመጣሉ፤በፊትህም ይሰግዳሉ፤+ለስምህም ክብር ይሰጣሉ።+ 10  አንተ ታላቅ ነህና፤ ድንቅ ነገሮችም ትሠራለህ፤+አንተ አምላክ ነህ፤ ከአንተ ሌላ የለም።+ 11  ይሖዋ ሆይ፣ መንገድህን አስተምረኝ።+ በእውነትህ እሄዳለሁ።+ ስምህን እፈራ ዘንድ ልቤን አንድ አድርግልኝ።*+ 12  ይሖዋ አምላኬ ሆይ፣ በሙሉ ልቤ አወድስሃለሁ፤+ስምህንም ለዘላለም ከፍ ከፍ አደርጋለሁ፤ 13  ለእኔ የምታሳየው ታማኝ ፍቅር ታላቅ ነውና፤ሕይወቴንም* ጥልቅ ከሆነው መቃብር* አድነሃል።+ 14  አምላክ ሆይ፣ እብሪተኛ ሰዎች በእኔ ላይ ተነስተዋል፤+የጨካኞች ቡድን ሕይወቴን* ይሻታል፤አንተንም ከምንም አልቆጠሩም።*+ 15  ይሖዋ ሆይ፣ አንተ ግን መሐሪና ሩኅሩኅ፣*ለቁጣ የዘገየህ እንዲሁም ታማኝ ፍቅርህና ታማኝነትህ* የበዛ አምላክ ነህ።+ 16  ወደ እኔ ተመልከት፤ ሞገስም አሳየኝ።+ ለአገልጋይህ ብርታትህን ስጠው፤+የሴት ባሪያህንም ልጅ አድን። 17  እኔን የሚጠሉ አይተው እንዲያፍሩ፣የጥሩነትህን ምልክት* አሳየኝ። ይሖዋ ሆይ፣ አንተ ረዳቴና አጽናኜ ነህና።

የግርጌ ማስታወሻ

ወይም “ጎንበስ ብለህ ስማኝ።”
ወይም “ነፍሴን።”
ወይም “የአገልጋይህን ነፍስ ደስ አሰኛት።”
ወይም “ነፍሴን ወደ አንተ አነሳለሁና።”
ወይም “ያልተከፋፈለ ልብ ስጠኝ።”
ወይም “ሲኦል።” የሰው ልጆችን ሁሉ መቃብር ያመለክታል። የቃላት መፍቻውን ተመልከት።
ወይም “ነፍሴንም።”
ወይም “ነፍሴን።”
ወይም “አንተንም በፊታቸው አላደረጉም።”
ወይም “ቸር።”
ወይም “እውነትህ።”
ወይም “ማስረጃ።”