ሚክያስ 3:1-12

  • መሪዎችና ነቢያት ተወገዙ (1-12)

    • ሚክያስ በይሖዋ መንፈስ አማካኝነት ኃይል ተሞላ (8)

    • “ካህናቷ በክፍያ ያስተምራሉ” (11)

    • “ኢየሩሳሌም የፍርስራሽ ክምር ትሆናለች” (12)

3  እንዲህ አልኩ፦ “እናንተ የያዕቆብ መሪዎችናየእስራኤል ቤት ገዢዎች፣ እባካችሁ ስሙ።+ ትክክል የሆነውን ነገር ማወቅ አይገባችሁም?   ሆኖም እናንተ መልካም የሆነውን ትጠላላችሁ፤+ ክፉ የሆነውን ደግሞ ትወዳላችሁ፤+የሕዝቤን ቆዳ ትገፍፋላችሁ፤ ሥጋቸውንም ከአጥንቶቻቸው ትለያላችሁ።+   የሕዝቤንም ሥጋ ትበላላችሁ፤+ቆዳቸውንም ትገፍፋላችሁ፤አጥንቶቻቸውንም ትሰባብራላችሁ፤+በድስት ውስጥ እንዳለ አጥንትና በአፍላል* ውስጥ እንዳለ ሥጋ ትቆራርጧቸዋላችሁ።   በዚያን ጊዜ እርዳታ ለማግኘት ወደ ይሖዋ ይጮኻሉ፤እሱ ግን አይመልስላቸውም። ክፉ ድርጊት በመፈጸማቸው፣+በዚያን ጊዜ ፊቱን ይሰውርባቸዋል።+   ሕዝቤ እንዲባዝን በሚያደርጉ፣+በጥርሳቸው ሲነክሱ*+ ‘ሰላም!’ እያሉ በሚያውጁ፣+አፋቸው ላይ የሚያደርጉት ነገር በማይሰጣቸው ሰው ሁሉ ላይ ግን ጦርነት በሚያውጁ* ነቢያት ላይ ይሖዋ እንዲህ ይላል   ‘ሌሊት ይመጣባችኋል፤+ ራእይም አታዩም፤+ጨለማ ብቻ ይሆንባችኋል፤ ሟርትም አታሟርቱም። ፀሐይ በነቢያቱ ላይ ትጠልቅባቸዋለች፤ቀኑም ወደ ጨለማ ይለወጥባቸዋል።+   ባለ ራእዮች ኀፍረት ይከናነባሉ፤+ሟርተኞችም ይዋረዳሉ። ከአምላክ ዘንድ መልስ ስለማይኖርሁሉም አፋቸውን* ይሸፍናሉ።’”   እኔ በበኩሌ ለያዕቆብ ዓመፁን፣ ለእስራኤልም ኃጢአቱን እንድነግርበይሖዋ መንፈስ ኃይልን፣ፍትሕንና ብርታትን ተሞልቻለሁ።   ፍትሕን የምትጸየፉና ቀና የሆነውን ነገር ሁሉ የምታጣምሙ፣+እናንተ የያዕቆብ ቤት መሪዎች፣የእስራኤልም ቤት ገዢዎች፣ እባካችሁ ይህን ስሙ፤+ 10  ጽዮንን ደም በማፍሰስ፣ ኢየሩሳሌምንም በዓመፅ የምትገነቡ፣ ስሙ።+ 11  መሪዎቿ* በጉቦ ይፈርዳሉ፤+ካህናቷ በክፍያ ያስተምራሉ፤+ነቢያቷም በገንዘብ* ያሟርታሉ።+ ያም ሆኖ “ይሖዋ ከእኛ ጋር አይደለም?+ ምንም ዓይነት ጥፋት አይደርስብንም”+ እያሉ በይሖዋ ይመካሉ።* 12  ስለዚህ በእናንተ የተነሳጽዮን እንደ እርሻ ትታረሳለች፤ኢየሩሳሌም የፍርስራሽ ክምር ትሆናለች፤+የቤቱም* ተራራ፣ በጫካ እንዳሉ ከፍ ያሉ ቦታዎች* ይሆናል።+

የግርጌ ማስታወሻ

ወይም “በትልቅ ድስት።”
“የሚያላምጡት ነገር ሲያገኙ” ማለትም ሊሆን ይችላል።
ቃል በቃል “ጦርነትን በሚቀድሱ።”
ወይም “አፍንጫቸው ሥር ያለውን ጢም።”
ወይም “በይሖዋ እንደሚመኩ ይናገራሉ።”
ወይም “በብር።”
ቃል በቃል “ራሶቿ።”
ወይም “የቤተ መቅደሱም።”
ወይም “በዛፍ እንደተሸፈነ ተረተር።”