ምሳሌ 25:1-28

  • ሚስጥር መጠበቅ (9)

  • የተመረጡ ቃላት (11)

  • “ባልንጀራህ ቤት እግር አታብዛ” (17)

  • በጠላት ራስ ላይ ፍም መከመር (21, 22)

  • መልካም ወሬ እንደ ቀዝቃዛ ውኃ ነው (25)

25  እነዚህም የይሁዳ ንጉሥ የሕዝቅያስ+ ሰዎች የጻፏቸው* የሰለሞን ምሳሌዎች ናቸው፦+   አንድን ጉዳይ መሰወር ለአምላክ ክብሩ ነው፤+ጉዳይን በሚገባ መመርመር ደግሞ ለነገሥታት ክብራቸው ነው።   ሰማያት ከፍ ያሉ እንደሆኑ፣ ምድርም ጥልቅ እንደሆነች ሁሉየንጉሥም ልብ አይመረመርም።   የብርን ቆሻሻ አስወግድ፤ሙሉ በሙሉም የጠራ ይሆናል።+   ክፉን ሰው ከንጉሥ ፊት አስወግድ፤ዙፋኑም በጽድቅ ይጸናል።+   በንጉሥ ፊት ራስህን ከፍ ከፍ አታድርግ፤+ታላላቅ ሰዎችም ባሉበት ስፍራ አትቀመጥ፤+   በተከበረ ሰው ፊት ከሚያዋርድህ እሱ ራሱ “ወደዚህ ከፍ በል” ቢልህ ይሻላልና።+   ክስ ለመመሥረት አትቸኩል፤የኋላ ኋላ ባልንጀራህ ቢያዋርድህ ምን ይውጥሃል?+   ከባልንጀራህ ጋር ስለ ራስህ ጉዳይ ተሟገት፤+ሆኖም በሚስጥር የተነገረህን ጉዳይ* አትግለጥ፤+ 10  አለዚያ የሚሰማህ ሰው ያዋርድሃል፤ያናፈስከውንም መጥፎ ወሬ* መመለስ አትችልም። 11  በተገቢው ጊዜ የተነገረ ቃልከብር በተሠራ ዕቃ ላይ* እንዳለ የወርቅ ፖም ነው።+ 12  በጥበብ ወቀሳ የሚሰጥ ሰው፣ የሚሰማ ጆሮ ላለውእንደ ወርቅ ጉትቻና ከጥሩ ወርቅ እንደተሠራ ጌጥ ነው።+ 13  ታማኝ መልእክተኛ ለላኩት ሰዎችበመከር ወቅት እንደሚገኝ የበረዶ ቅዝቃዜ ነው፤የጌታውን መንፈስ* ያድሳልና።+ 14  የማይሰጠውን ስጦታ* እሰጣለሁ እያለ ጉራውን የሚነዛ ሰውዝናብ እንደማያመጣ ደመናና ነፋስ ነው።+ 15  በትዕግሥት አዛዥን ማሸነፍ ይቻላል፤ለስላሳም አንደበት* አጥንትን ይሰብራል።+ 16  ማር ካገኘህ የሚበቃህን ያህል ብቻ ብላ፤ከልክ በላይ ከበላህ ሊያስመልስህ ይችላልና።+ 17  እንዳይሰለችህና እንዳይጠላህወደ ባልንጀራህ ቤት እግር አታብዛ። 18  በባልንጀራው ላይ በሐሰት የሚመሠክርእንደ ቆመጥ፣ እንደ ሰይፍና እንደ ሹል ፍላጻ ነው።+ 19  በችግር ወቅት እምነት በማይጣልበት* ሰው መተማመን፣እንደተሰበረ ጥርስና እንደሰለለ እግር ነው። 20  ላዘነ ልብ የሚዘምር ሰው፣በብርድ ቀን ልብሱን እንደሚያወልቅ፣በሶዳም ላይ እንደተጨመረ ኮምጣጤ ነው።+ 21  ጠላትህ* ቢራብ ምግብ ስጠው፤ቢጠማ ውኃ ስጠው፤+ 22  ይህን ብታደርግ በራሱ ላይ ፍም ትከምራለህና፤*+ይሖዋም ወሮታ ይከፍልሃል። 23  የሰሜን ነፋስ ኃይለኛ ዝናብ ያመጣል፤ሐሜተኛ ምላስም የሰውን ፊት ያስቆጣል።+ 24  ከጨቅጫቃ* ሚስት ጋር በአንድ ቤት ከመኖርበጣሪያ ማዕዘን ላይ መኖር ይሻላል።+ 25  ቀዝቃዛ ውኃ የዛለችን ነፍስ* እንደሚያረካ ሁሉከሩቅ አገር የመጣ መልካም ወሬም እንዲሁ ነው።+ 26  ለክፉ ሰው የሚንበረከክ* ጻድቅ፣እንደጨቀየ ምንጭና እንደተበከለ የውኃ ጉድጓድ ነው። 27  ብዙ ማር መብላት ጥሩ አይደለም፤+የራስንም ክብር መሻት አያስከብርም።+ 28  ስሜቱን መቆጣጠር የማይችል ሰው*ቅጥር እንደሌላት የፈረሰች ከተማ ነው።+

የግርጌ ማስታወሻ

ወይም “የገለበጧቸውና ያጠናቀሯቸው።”
ወይም “የሌሎችን ሚስጥር።”
ወይም “ተንኮል ያዘለ አሉባልታ።”
ወይም “በብር መደብ ላይ።”
ወይም “ነፍስ።”
ቃል በቃል “የውሸት ስጦታ።”
ወይም “የለዘበም አንደበት።”
“በከዳተኛ” ማለትም ሊሆን ይችላል።
ቃል በቃል “የሚጠላህ ሰው።”
የሰውየውን ልብ ለማለስለስና ግትር አቋሙን ለማለዘብ የሚደረግን ጥረት ያመለክታል።
ወይም “ከነዝናዛ።”
ወይም “በክፉ ሰው ፊት አቋሙን የሚያላላ።” ቃል በቃል “በክፉ ሰው ፊት የሚንገዳገድ።”
ወይም “መንፈሱን የማይገታ ሰው።”