ለዮሐንስ የተገለጠለት ራእይ 20:1-15

  • ሰይጣን ለ1,000 ዓመት ታሰረ (1-3)

  • ከክርስቶስ ጋር ለ1,000 ዓመት ይገዛሉ (4-6)

  • ሰይጣን ይፈታል፤ ከዚያም ይጠፋል (7-10)

  • ሙታን በነጩ ዙፋን ፊት ፍርድ ተሰጣቸው (11-15)

20  እኔም የጥልቁን ቁልፍና+ ታላቅ ሰንሰለት በእጁ የያዘ አንድ መልአክ ከሰማይ ሲወርድ አየሁ።  እሱም ዘንዶውን+ ያዘውና ለ1,000 ዓመት አሰረው፤ ይህም ዘንዶ ዲያብሎስና+ ሰይጣን+ የሆነው የጥንቱ እባብ+ ነው።  ደግሞም ይህ 1,000 ዓመት እስኪያበቃ ድረስ ከእንግዲህ ሕዝቦችን እንዳያሳስት ወደ ጥልቁ+ ወረወረውና ዘጋበት፤ በማኅተምም አሸገው። ከዚያ በኋላ ለጥቂት ጊዜ ሊፈታ ይገባዋል።+  ዙፋኖችንም አየሁ፤ በዙፋኖቹም ላይ ለተቀመጡት የመፍረድ ሥልጣን ተሰጣቸው። ስለ ኢየሱስ በመመሥከራቸውና ስለ አምላክ በመናገራቸው የተነሳ የተገደሉትን* ሰዎች ነፍሳት* እንዲሁም አውሬውን ወይም ምስሉን ያላመለኩትንና ምልክቱን በግንባራቸውም ሆነ በእጃቸው ላይ ያልተቀበሉትን ሰዎች አየሁ።+ እነሱም ሕያው ሆነው ከክርስቶስ ጋር ለ1,000 ዓመት ነገሡ።+  (የቀሩት ሙታን+ ይህ 1,000 ዓመት እስኪያበቃ ድረስ ሕያው አልሆኑም።) ይህ የመጀመሪያው ትንሣኤ ነው።+  በመጀመሪያው ትንሣኤ ተካፋይ የሆኑ ሁሉ ደስተኞችና ቅዱሳን ናቸው፤+ ሁለተኛው ሞት+ በእነዚህ ላይ ሥልጣን የለውም፤+ ከዚህ ይልቅ የአምላክና የክርስቶስ ካህናት ይሆናሉ፤+ ከእሱም ጋር ለ1,000 ዓመት ይነግሣሉ።+  ይህ 1,000 ዓመት እንዳበቃም ሰይጣን ከእስራቱ ይፈታል፤  እሱም በአራቱም የምድር ማዕዘናት ያሉትን ብሔራት፣ ጎግንና ማጎግን ለማሳሳትና ለጦርነቱ አንድ ላይ ለመሰብሰብ ይወጣል። የእነዚህም ቁጥር በባሕር ዳር እንዳለ አሸዋ ነው።  እነሱም በምድር ሁሉ ተሰራጩ፤ እንዲሁም የቅዱሳኑን ሰፈርና የተወደደችውን ከተማ ከበቡ። ሆኖም እሳት ከሰማይ ወርዶ በላቸው።+ 10  ሲያሳስታቸው የነበረው ዲያብሎስም፣ አውሬውና+ ሐሰተኛው ነቢይ ወዳሉበት ወደ እሳቱና ወደ ድኙ ሐይቅ ተወረወረ፤+ እነሱም ለዘላለም ቀንና ሌሊት ይሠቃያሉ።* 11  እኔም አንድ ትልቅ ነጭ ዙፋንና በዙፋኑ ላይ የተቀመጠውን አየሁ።+ ምድርና ሰማይ ከፊቱ ሸሹ፤+ ስፍራም አልተገኘላቸውም። 12  ከዚያም ሙታንን፣ ታላላቆችንና ታናናሾችን በዙፋኑ ፊት ቆመው አየሁ፤ የመጽሐፍ ጥቅልሎችም ተከፈቱ። ሌላም ጥቅልል ተከፈተ፤ ይህም የሕይወት መጽሐፍ ጥቅልል ነው።+ ሙታን በጥቅልሎቹ ውስጥ በተጻፉት ነገሮች መሠረት እንደየሥራቸው ፍርድ ተሰጣቸው።+ 13  ባሕርም በውስጡ ያሉትን ሙታን ሰጠ፤ ሞትና መቃብርም* በውስጣቸው ያሉትን ሙታን ሰጡ፤ እነሱም እያንዳንዳቸው እንደየሥራቸው ፍርድ ተሰጣቸው።+ 14  ሞትና መቃብርም* ወደ እሳቱ ሐይቅ ተወረወሩ።+ ይህም የእሳት ሐይቅ+ ሁለተኛውን ሞት ያመለክታል።+ 15  በተጨማሪም በሕይወት መጽሐፍ+ ላይ ተጽፎ ያልተገኘ ሁሉ ወደ እሳቱ ሐይቅ ተወረወረ።+

የግርጌ ማስታወሻ

ቃል በቃል “በመጥረቢያ የተቀሉትን።”
የቃላት መፍቻውንራእይ 6:9 ላይ የሚገኘውን የግርጌ ማስታወሻ ተመልከት።
ወይም “ቀንና ሌሊት ይታገታሉ፤ ቀንና ሌሊት ይታሰራሉ።”
ወይም “ሐዲስም።” የሰው ልጆችን ሁሉ መቃብር ያመለክታል። የቃላት መፍቻውን ተመልከት።
ወይም “ሐዲስም።” የሰው ልጆችን ሁሉ መቃብር ያመለክታል። የቃላት መፍቻውን ተመልከት።