አሞጽ 1:1-15

  • አሞጽ ከይሖዋ የተቀበለው መልእክት (1, 2)

  • በተደጋጋሚ በተፈጸመ ዓመፅ የተነሳ የተላለፈ ፍርድ (3-15)

    • ሶርያ (3-5)፣ ፍልስጤም (6-8)፣ ጢሮስ (9, 10)፣ ኤዶም (11, 12)፣ አሞን (13-15)

1  በይሁዳ ንጉሥ በዖዝያና+ በእስራኤል ንጉሥ በዮአስ+ ልጅ በኢዮርብዓም+ ዘመን፣ የመሬት መንቀጥቀጡ+ ከመከሰቱ ከሁለት ዓመት በፊት በተቆአ+ ከነበሩት በግ አርቢዎች መካከል አንዱ ለሆነው ለአሞጽ* ስለ እስራኤል በራእይ የተገለጠለት ቃል።  እሱ እንዲህ ብሏል፦ “ይሖዋ ከጽዮን እንደ አንበሳ ያገሳል፤ከኢየሩሳሌምም ድምፁን በኃይል ያሰማል። የእረኞቹ ማሰማሪያዎች ያለቅሳሉ፤የቀርሜሎስም አናት ይደርቃል።”+   “ይሖዋ እንዲህ ይላል፦‘“ስለ ሦስቱ የደማስቆ ዓመፅ* ብሎም ስለ አራቱ እጄን አልመልስም፤ምክንያቱም በብረት ማሄጃ ጊልያድን ወቅተዋል።+   በመሆኑም በሃዛኤል+ ቤት ላይ እሳት እሰዳለሁ፤የቤንሃዳድንም የማይደፈሩ ማማዎች ይበላል።+   የደማስቆን በሮች መቀርቀሪያ እሰብራለሁ፤+የቢቃትአዌን ነዋሪዎችን አጠፋለሁ፤በቤትኤደን ተቀምጦ የሚገዛውን* አስወግዳለሁ፤የሶርያ ሰዎችም ወደ ቂር በግዞት ይሄዳሉ”+ ይላል ይሖዋ።’   ይሖዋ እንዲህ ይላል፦‘“ስለ ሦስቱ የጋዛ ዓመፅ+ ብሎም ስለ አራቱ እጄን አልመልስም፤ምክንያቱም ሕዝቡን ሁሉ ማርከው+ ለኤዶም አሳልፈው ሰጥተዋል።   በመሆኑም በጋዛ ቅጥር ላይ እሳት እሰዳለሁ፤+የማይደፈሩ ማማዎቿንም ይበላል።   የአሽዶድን ነዋሪዎች አጠፋለሁ፤+በአስቀሎን ተቀምጦ የሚገዛውንም* አስወግዳለሁ፤+እጄን በኤቅሮን ላይ እዘረጋለሁ፤+የተረፉት ፍልስጤማውያንም ይጠፋሉ”+ ይላል ሉዓላዊው ጌታ ይሖዋ።’   ይሖዋ እንዲህ ይላል፦‘ስለ ሦስቱ የጢሮስ ዓመፅ+ ብሎም ስለ አራቱ እጄን አልመልስም፤ምክንያቱም ሕዝቡን ሁሉ ማርከው ለኤዶም አሳልፈው ሰጥተዋል፤ደግሞም የወንድማማቾችን ቃል ኪዳን አላስታወሱም።+ 10  በመሆኑም በጢሮስ ቅጥር ላይ እሳት እሰዳለሁ፤የማይደፈሩ ማማዎቿንም ይበላል።’+ 11  ይሖዋ እንዲህ ይላል፦‘ስለ ሦስቱ የኤዶም ዓመፅ+ ብሎም ስለ አራቱ እጄን አልመልስም፤ምክንያቱም የገዛ ወንድሙን በሰይፍ አሳዷል፤+ምሕረት ለማሳየትም እንቢተኛ ሆኗል፤በቁጣው ያላንዳች ፋታ ይዘነጣጥላቸዋል፤አሁንም ቢሆን በእነሱ ላይ ቁጣው አልበረደም።+ 12  በመሆኑም በቴማን+ ላይ እሳት እሰዳለሁ፤የቦስራንም የማይደፈሩ ማማዎች ይበላል።’+ 13  “ይሖዋ እንዲህ ይላል፦‘“ስለ ሦስቱ የአሞናውያን ዓመፅ+ ብሎም ስለ አራቱ እጄን አልመልስም፤ምክንያቱም ግዛታቸውን ለማስፋት ሲሉ የጊልያድን ነፍሰ ጡር ሴቶች ሆድ ቀደዋል።+ 14  በመሆኑም በራባ ቅጥር ላይ እሳት እሰዳለሁ፤+የማይደፈሩ ማማዎቿንም ይበላል፤በውጊያው ቀን ቀረርቶ ይሰማል፤አውሎ ነፋስ በሚነሳበትም ቀን ነውጥ ይኖራል። 15  ንጉሣቸውም ከመኳንንቱ ጋር በግዞት ይወሰዳል”+ ይላል ይሖዋ።’

የግርጌ ማስታወሻ

“ሸክም መሆን” ወይም “ሸክም መሸከም” የሚል ትርጉም አለው።
ወይም “ወንጀል።”
ቃል በቃል “በትረ መንግሥቱን የያዘውን።”
ቃል በቃል “በትረ መንግሥቱን የያዘውንም።”