ኢሳይያስ 32:1-20
32 እነሆ፣ ንጉሥ+ ለጽድቅ ይነግሣል፤+መኳንንትም ፍትሕ ለማስፈን ይገዛሉ።
2 እያንዳንዱም ከነፋስ እንደ መከለያ፣*ከውሽንፍር እንደ መሸሸጊያ፣*ውኃ በሌለበት ምድር እንደ ጅረት፣+በደረቅ ምድርም እንደ ትልቅ ቋጥኝ ጥላ ይሆናል።
3 በዚያ ጊዜ፣ የሚያዩ ሰዎች ዓይኖች አይጨፈኑም፤የሚሰሙ ሰዎችም ጆሮዎች በትኩረት ያዳምጣሉ።
4 የችኩሎች ልብ እውቀትን ያሰላስላል፤የሚንተባተብ ምላስም አቀላጥፎና አጥርቶ ይናገራል።+
5 የማመዛዘን ችሎታ የጎደለው ሰው ከእንግዲህ ለጋስ አይባልም፤ሥርዓት የሌለው ሰውም ትልቅ ሰው አይባልም፤
6 የማመዛዘን ችሎታ የጎደለው ሰው የማይረባ ነገር ይናገራልና፤ደግሞም በይሖዋ ላይ ክህደት ለመፈጸምና* የውሸት ቃል ለመናገር፣እንዲሁም የተራበ ሰው የሚበላ ነገር እንዳያገኝና*የተጠማ ሰው የሚጠጣ ነገር እንዳያገኝ ለማድረግልቡ ክፋትን ያውጠነጥናል።+
7 ሥርዓት የሌለው ሰው የሚጠቀምባቸው ዘዴዎች መጥፎ ናቸው፤+ድሃው ትክክል የሆነውን ነገር በሚናገርበት ጊዜም እንኳየተጎሳቆለውን ሰው በውሸት ቃል ለማጥፋትአሳፋሪ ለሆነ ምግባር ድጋፍ ይሰጣል።+
8 ለጋስ ሰው ግን ስለ ልግስና ያስባል፤ዘወትር የልግስና* ተግባር ለመፈጸም ይተጋል።
9 “እናንተ ደንታ ቢስ ሴቶች፣ ተነሱ፤ ድምፄንም ስሙ!
እናንተ ግድየለሽ ሴቶች ልጆች፣+ የምናገረውን ነገር በትኩረት አዳምጡ!
10 እናንተ ግድየለሾች፣ ከአንድ ዓመት ብዙም ባልበለጠ ጊዜ ውስጥ ትሸበራላችሁ፤ምክንያቱም የወይን ፍሬ የምትለቅሙበት ጊዜ ሲያልፍ የተሰበሰበ ፍሬ አይኖርም።+
11 እናንተ ደንታ ቢስ ሴቶች፣ ተንቀጥቀጡ!
እናንተ ግድየለሾች፣ ተሸበሩ!
ልብሳችሁን በሙሉ አውልቁ፤በወገባችሁም ላይ ማቅ ታጠቁ።+
12 ስለ መልካሙ እርሻና ፍሬያማ ስለሆነው ወይንበሐዘን ደረታችሁን ምቱ።
13 የሕዝቤን ምድር እሾህና አሜኬላ ይወርሱታልና፤በደስታ ተሞልተው የነበሩትን ቤቶች ሁሉ፣አዎ፣ በሐሴት ተሞልታ የነበረችውን ከተማ ይሸፍናሉ።+
14 የማይደፈረው ማማ ባዶ ሆኗልና፤ሁካታ የነበረበት ከተማ ወና ቀርቷል።+
ኦፌልና+ መጠበቂያ ግንቡ ለዘለቄታው ጠፍ ሆነዋል፤የዱር አህዮች መፈንጫናየመንጎች መሰማሪያ ሆነዋል፤+
15 ይህም የሚሆነው መንፈስ ከላይ እስኪፈስብን፣+ምድረ በዳውም የፍራፍሬ እርሻ እስከሚሆን፣የፍራፍሬ እርሻውም እንደ ጫካ እስከሚቆጠር ድረስ ነው።+
16 ከዚያም በምድረ በዳ ፍትሕ ይሰፍናል፤በፍራፍሬ እርሻም ጽድቅ ይኖራል።+
17 የእውነተኛ ጽድቅ ውጤት ሰላም፣+የእውነተኛ ጽድቅ ፍሬም ዘላቂ ጸጥታና ደህንነት ይሆናል።+
18 ሕዝቤ ሰላማዊ በሆነ የመኖሪያ ስፍራ፣አስተማማኝ በሆነ መኖሪያና ጸጥታ በሰፈነበት የማረፊያ ቦታ ይኖራል።+
19 ሆኖም በረዶው ጫካውን ያወድማል፤ከተማዋም ሙሉ በሙሉ ትፈራርሳለች።
20 እናንተ በውኃዎች ሁሉ ዳር ዘር የምትዘሩ፣በሬውንና አህያውንም የምትለቁ* ደስተኞች ናችሁ።”+