ኢሳይያስ 60:1-22

  • የይሖዋ ክብር በጽዮን ላይ ያበራል (1-22)

    • ‘ወደ ቤታቸው እንደሚተሙ ርግቦች’ (8)

    • በመዳብ ፋንታ ወርቅ (17)

    • ‘ጥቂት የሆነው ሺህ ይሆናል’ (22)

60  “አንቺ ሴት ሆይ፣ ተነሺ፣+ ብርሃን አብሪ፤ ብርሃንሽ መጥቷልና። የይሖዋ ክብር በአንቺ ላይ ያበራል።+   እነሆ፣ ጨለማ ምድርን፣ድቅድቅ ጨለማም ብሔራትን ይሸፍናል፤በአንቺ ላይ ግን ይሖዋ ያበራል፤ክብሩም በአንቺ ላይ ይታያል።   ብሔራት ወደ ብርሃንሽ፣+ነገሥታትም+ አንጸባራቂ ወደሆነው ውበትሽ* ይመጣሉ።+   ዓይንሽን አንስተሽ ዙሪያሽን ተመልከቺ! ሁሉም አንድ ላይ ተሰብስበዋል፤ ወደ አንቺም እየመጡ ነው። ከሩቅ ቦታ ወንዶች ልጆችሽ በመምጣት ላይ ናቸው፤+ሴቶች ልጆችሽም ታዝለው እየመጡ ነው።+   በዚያን ጊዜ ታያለሽ፤ ፊትሽም ይፈካል፤+ልብሽ በኃይል ይመታል፤ በደስታም ይሞላል፤ምክንያቱም የባሕር ብልጽግና ወደ አንቺ ይጎርፋል፤የብሔራትም ሀብት ወደ አንቺ ይመጣል።+   የግመል መንጋ ምድርሽን ይሸፍናል፤*የምድያምና የኤፋ+ ግልገል ግመሎች ያጥለቀልቁሻል። ሁሉም ወርቅና ነጭ ዕጣን ይዘውከሳባ ይመጣሉ። የይሖዋንም ውዳሴ ያውጃሉ።+   የቄዳር+ መንጎች ሁሉ ወደ አንቺ ይሰበሰባሉ። የነባዮት+ አውራ በጎች ያገለግሉሻል። እነሱም በመሠዊያዬ ላይ ተቀባይነት ያለው መሥዋዕት ይሆናሉ፤+ክብራማ የሆነውንም ቤቴን* አሳምረዋለሁ።+   እንደ ደመና፣ ወደ ቤታቸውም* እንደሚተሙ ርግቦችእየበረሩ የሚመጡት እነዚህ እነማን ናቸው?   ደሴቶች እኔን ተስፋ ያደርጋሉና፤+የተርሴስ መርከቦችም ከሩቅ ወንዶች ልጆችሽንከነብራቸውና ከነወርቃቸውለአምላክሽ ለይሖዋ ስምና ለእስራኤል ቅዱስ ለማምጣት+ቀዳሚ ሆነው* ይወጣሉ፤እሱ ክብር* ያጎናጽፍሻልና።+ 10  የባዕድ አገር ሰዎች ቅጥሮችሽን ይገነባሉ፤ነገሥታታቸውም ያገለግሉሻል፤+በቁጣዬ መትቼሻለሁና፤በሞገሴ* ግን ምሕረት አሳይሻለሁ።+ 11  በሮችሽ ሁልጊዜ ክፍት ይሆናሉ፤+የብሔራትን ሀብት ወደ አንቺ ያመጡ ዘንድበሮችሽ ቀንም ሆነ ሌሊት አይዘጉም፤ነገሥታታቸውም ቀዳሚ ይሆናሉ።+ 12  አንቺን የማያገለግል ማንኛውም ብሔርም ሆነ ማንኛውም መንግሥት ይጠፋልና፤ብሔራትም ፈጽመው ይደመሰሳሉ።+ 13  የመቅደሴን ስፍራ አስውብ ዘንድየሊባኖስ ክብር፣+ ጥዱ፣ የአሽ ዛፉና* የፈረንጅ ጥዱበአንድነት ወደ አንቺ ይመጣሉ፤+እግሬ የሚያርፍበትንም ስፍራ አከብራለሁ።+ 14  የጨቋኞችሽ ወንዶች ልጆች መጥተው በፊትሽ ይሰግዳሉ፤የሚያዋርዱሽ ሁሉ እግርሽ ሥር ይደፋሉ፤ደግሞም የይሖዋ ከተማ፣የእስራኤልም ቅዱስ አምላክ ንብረት የሆንሽ ጽዮን ብለው ይጠሩሻል።+ 15  የተተውሽና የተጠላሽ፣ ማንም ሰው የማያልፍብሽ መሆንሽ ቀርቶ+የዘላለም መኩሪያ፣ከትውልድ እስከ ትውልድም የደስታ ምንጭ እንድትሆኚ አደርግሻለሁ።+ 16  አንቺም የብሔራትን ወተት ትጠጫለሽ፤+የነገሥታትን ጡት ትጠቢያለሽ፤+እኔ ይሖዋ አዳኝሽ እንደሆንኩ፣ደግሞም የያዕቆብ ኃያል አምላክ የሆንኩት እኔ እንደምቤዥሽ በእርግጥ ታውቂያለሽ።+ 17  በመዳብ ፋንታ ወርቅ፣በብረት ፋንታ ብር፣በእንጨት ፋንታ መዳብ፣በድንጋዮችም ፋንታ ብረት አመጣለሁ፤ሰላምንም የበላይ ተመልካቾችሽ፣ጽድቅንም አሠሪዎችሽ አድርጌ እሾማለሁ።+ 18  ከዚህ በኋላ በምድርሽ ውስጥ ዓመፅ፣ወይም በክልልሽ ውስጥ ጥፋትና ውድመት አይሰማም።+ ቅጥሮችሽን መዳን፣+ በሮችሽንም ውዳሴ ብለሽ ትጠሪያቸዋለሽ። 19  ከእንግዲህ ፀሐይ በቀን ብርሃን አትሆንልሽም፤የጨረቃም ብርሃን ከእንግዲህ አያበራልሽም፤ይሖዋ የዘላለም ብርሃን፣+አምላክሽም ውበት ይሆንልሻልና።+ 20  ፀሐይሽ ከእንግዲህ አትጠልቅም፤ጨረቃሽም አትደበዝዝም፤ይሖዋ የዘላለም ብርሃን ይሆንልሻልና፤+የሐዘንሽም ጊዜ ያበቃል።+ 21  ሕዝቦችሽም ሁሉ ጻድቃን ይሆናሉ፤ምድሪቱን ለዘላለም ይወርሳሉ። እነሱ፣ ውበት እጎናጸፍ ዘንድ የተከልኳቸው ችግኞች፣የእጆቼም ሥራ ናቸው።+ 22  ጥቂት የሆነው ሺህ፣ትንሽ የሆነውም ኃያል ብሔር ይሆናል። እኔ ይሖዋ፣ ይህን በራሱ ጊዜ አፋጥነዋለሁ።”

የግርጌ ማስታወሻ

ወይም “ወደ ንጋትሽ ጸዳል።”
ቃል በቃል “ይሸፍንሻል።”
ወይም “የውበት ቤቴን።”
ወይም “ወደ ጎጇቸውም መግቢያ።”
ወይም “ውበት።”
ወይም “እንደቀድሞው።”
ወይም “በበጎ ፈቃዴ።”
እስከ 15 ሜትር የሚደርስ ርዝመት ያለው ትልቅ ዛፍ ነው። ቅጠሎቹ ፈዘዝ ያለ አረንጓዴ ቀለም ያላቸው ሲሆን ቅርንጫፎቹ ደግሞ አመድማ መልክ አላቸው።