ኢዩኤል 3:1-21

  • ይሖዋ በብሔራት ሁሉ ላይ ይፈርዳል (1-17)

    • የኢዮሳፍጥ ሸለቆ (2, 12)

    • የፍርድ ውሳኔ የሚሰጥበት ሸለቆ (14)

    • ይሖዋ ለእስራኤል ምሽግ ይሆናል (16)

  • ይሖዋ ሕዝቡን ይባርካል (18-21)

3  “እነሆ፣ በዚያ ዘመንና በዚያ ጊዜየይሁዳንና የኢየሩሳሌምን ምርኮኞች ስመልስ፣+   ብሔራትን ሁሉ ሰብስቤወደ ኢዮሳፍጥ* ሸለቆ* አወርዳቸዋለሁ። ለሕዝቤና ርስቴ ለሆነው ለእስራኤል ስልበዚያ ከእነሱ ጋር እፋረዳለሁ፤+በብሔራት መካከል በትነዋቸዋልና፤ደግሞም ምድሬን ተከፋፍለዋታል።+   በሕዝቤ ላይ ዕጣ ይጣጣላሉና፤+ዝሙት አዳሪ ለማግኘት ሲሉ ወንድ ልጅን አሳልፈው ይሰጣሉ፤የወይን ጠጅ ለመጠጣት ሲሉም ሴት ልጅን ይሸጣሉ።   ጢሮስ፣ ሲዶና እና የፍልስጤም ግዛቶች ሁሉ፣ከእኔ ጋር ምን ጉዳይ አላችሁ? ላደረግኩባችሁ ነገር ብድራት ልትመልሱልኝ ነው? ብድራት የምትመልሱልኝ ከሆነብድራታችሁን ወዲያውኑ፣ በፍጥነት በራሳችሁ ላይ እመልሳለሁ።+   ምክንያቱም እናንተ ብሬንና ወርቄን ወስዳችኋል፤+እጅግ ምርጥ የሆነውን ውድ ንብረቴንም ወደ ቤተ መቅደሶቻችሁ አስገብታችኋል፤   ደግሞም ከምድራቸው ርቀው እንዲሄዱ ለማድረግ ስትሉየይሁዳንና የኢየሩሳሌምን ሕዝብ ለግሪኮች ሸጣችሁ፤+   እነሆ፣ እነሱን ከሸጣችሁባቸው ቦታዎች እንዲመለሱ አነሳሳቸዋለሁ፤+ብድራታችሁንም በራሳችሁ ላይ እመልሳለሁ።   ወንዶችና ሴቶች ልጆቻችሁን ለይሁዳ ሕዝብ እሸጣለሁ፤+እነሱም በሩቅ ላለ ብሔር ይኸውም ለሳባ ሰዎች ይሸጧቸዋል፤ይሖዋ ራሱ ይህን ተናግሯልና።   በብሔራት መካከል ይህን አውጁ፦+ ‘ለጦርነት ተዘጋጁ!* ኃያላን ሰዎችን አነሳሱ! ወታደሮቹ ሁሉ ቀርበው ጥቃት ይሰንዝሩ!+ 10  ማረሻችሁን ሰይፍ፣ ማጭዳችሁንም ጦር ለማድረግ ቀጥቅጡ። ደካማው ሰው “እኔ ብርቱ ነኝ” ይበል። 11  እናንተ ዙሪያውን ያላችሁ ብሔራት ሁሉ፣ ኑና ተረዳዱ፤ አንድ ላይም ተሰብሰቡ!’”+ ይሖዋ ሆይ፣ ኃያላንህን* ወደዚያ ቦታ አውርድ። 12  “ብሔራት ይነሱና ወደ ኢዮሳፍጥ ሸለቆ* ይምጡ፤ዙሪያውን ባሉት ብሔራት ሁሉ ላይ ለመፍረድ በዚያ እቀመጣለሁና።+ 13  መከሩ ስለደረሰ ማጭድ ስደዱ። የወይን መጭመቂያው ስለሞላ ኑ፣ ወርዳችሁ እርገጡ።+ ማጠራቀሚያዎቹ ሞልተው አፍስሰዋል፤ ክፋታቸው እጅግ በዝቷልና። 14  ብዙ ሕዝብ፣ በጣም ብዙ ሕዝብ የፍርድ ውሳኔ በሚሰጥበት ሸለቆ* ተሰብስቧል፤የፍርድ ውሳኔ በሚሰጥበት ሸለቆ* የይሖዋ ቀን ቀርቧልና።+ 15  ፀሐይና ጨረቃ ይጨልማሉ፤ከዋክብትም ብርሃናቸውን አይሰጡም። 16  ይሖዋም ከጽዮን እንደ አንበሳ ያገሳል፤ከኢየሩሳሌም ድምፁን በኃይል ያሰማል። ሰማይና ምድር ይናወጣሉ፤ይሖዋ ግን ለሕዝቡ መጠጊያ፣+ለእስራኤል ሕዝብ ምሽግ ይሆናል። 17  እናንተም እኔ በተቀደሰው ተራራዬ+ በጽዮን የምኖር አምላካችሁ ይሖዋ እንደሆንኩ ታውቃላችሁ። ኢየሩሳሌም ቅዱስ ስፍራ ትሆናለች፤+እንግዶችም* ከእንግዲህ በእሷ አያልፉም።+ 18  በዚያ ቀን ተራሮቹ ጣፋጭ የወይን ጠጅ ያንጠባጥባሉ፤+ኮረብቶቹ ወተት ያፈሳሉ፤የይሁዳ ጅረቶችም ሁሉ በውኃ ይሞላሉ። ከይሖዋም ቤት ምንጭ ይፈልቃል፤+የሺቲምንም* ሸለቆ* ያጠጣል። 19  ግብፅ ግን ባድማ ትሆናለች፤+ኤዶምም በምድራቸው ንጹሕ ደም በማፍሰስ+በይሁዳ ሕዝብ ላይ ግፍ ስለፈጸመች+ጠፍ ምድረ በዳ ትሆናለች።+ 20  ይሁንና ይሁዳ ምንጊዜም፣ኢየሩሳሌምም ከትውልድ እስከ ትውልድ የሰው መኖሪያ ትሆናለች።+ 21  ንጹሕ አድርጌ ያልቆጠርኩትን ደማቸውን* ንጹሕ አድርጌ እቆጥረዋለሁ፤+ይሖዋም በጽዮን ይኖራል።”+

የግርጌ ማስታወሻ

“ይሖዋ ፈራጅ ነው” የሚል ትርጉም አለው።
ወይም “ረባዳማ ሜዳ።”
ቃል በቃል “ጦርነትን ቀድሱ!”
ወይም “ይሖዋ ሆይ፣ ተዋጊዎችህን።”
ወይም “ረባዳማ ሜዳ።”
ወይም “ረባዳማ ሜዳ።”
ወይም “ረባዳማ ሜዳ።”
ወይም “ባዕዳንም።”
ወይም “ደረቅ ወንዝ።”
“የግራር ዛፎች” የሚል ትርጉም አለው።
ወይም “የደም ዕዳቸውን።”