ኢዮብ 19:1-29

  • ኢዮብ የሰጠው መልስ (1-29)

    • “የጓደኞቹን” ተግሣጽ ተቃወመ (1-6)

    • ሰዎች እንደራቁት ተናገረ (13-19)

    • ‘የሚዋጀኝ ሕያው ነው’ (25)

19  ኢዮብ እንዲህ ሲል መለሰ፦   “እናንተ ሰዎች ነፍሴን የምታበሳጯት፣*+በቃላት የምትደቁሱኝስ+ እስከ መቼ ነው?   ይኸው አሥር ጊዜ ገሠጻችሁኝ፤*ከባድ በደል ስትፈጽሙብኝ አላፈራችሁም።+   ስህተት ብፈጽምም እንኳ፣የሠራሁት ስህተት ከእኔ ጋር ይኖራል።   በእኔ ላይ የደረሰው ነቀፋ ተገቢ እንደሆነ አድርጋችሁ በመከራከር፣በእኔ ላይ ራሳችሁን ከፍ ከፍ ብታደርጉ፣   ያሳተኝ አምላክ እንደሆነ እወቁ፤በማጥመጃ መረቡም ይዞኛል።   እነሆ ‘ግፍ ተፈጸመብኝ!’ ብዬ ብጮኽም መልስ አላገኘሁም፤+እርዳታ ለማግኘት ብጣራም ፍትሕ የለም።+   መንገዴን በድንጋይ ግንብ ዘጋ፤ እኔም ማለፍ አልቻልኩም፤ጎዳናዬንም በጨለማ ጋረደ።+   ክብሬን ገፎኛል፤አክሊሉንም ከራሴ ላይ አንስቷል። 10  እስክጠፋ ድረስ በሁሉም አቅጣጫ አፈራረሰኝ፤ተስፋዬን እንደ ዛፍ ነቀለው። 11  ቁጣው በእኔ ላይ ነደደ፤እንደ ጠላቱም ቆጠረኝ።+ 12  ሠራዊቱ በአንድነት መጥተው ከበቡኝ፤በድንኳኔም ዙሪያ ሰፈሩ። 13  የገዛ ወንድሞቼን ከእኔ አራቀ፤የሚያውቁኝም ሰዎች ጥለውኝ ሄዱ።+ 14  የቅርብ ወዳጆቼ ትተውኛል፤*በደንብ የማውቃቸውም ሰዎች ረሱኝ።+ 15  በቤቴ ያሉ እንግዶችና+ ሴቶች ባሪያዎቼ እንደ መጤ ቆጠሩኝ፤እንደ ባዕድ አገር ሰው ተመለከቱኝ። 16  አገልጋዬን ጠራሁት፤ እሱ ግን አልመለሰልኝም፤እንዲራራልኝ በአንደበቴ ለመንኩት። 17  ሚስቴ ትንፋሼን እንኳ ተጸየፈችው፤+ለገዛ ወንድሞቼም* መጥፎ ጠረን ሆንኩባቸው። 18  ትናንሽ ልጆች እንኳ ናቁኝ፤ስነሳ በእኔ ላይ ያላግጣሉ። 19  የቅርብ ወዳጆቼ ሁሉ ተጸየፉኝ፤+የምወዳቸውም ሰዎች በእኔ ላይ ተነሱ።+ 20  አጥንቶቼ ከቆዳዬና ከሥጋዬ ጋር ተጣበቁ፤+ከሞት ለጥቂት* ተረፍኩ። 21  ወዳጆቼ ሆይ፣ ማሩኝ፤ እባካችሁ ማሩኝ፤የአምላክ እጅ መታኛለችና።+ 22  አምላክ እንዳሳደደኝ የምታሳድዱኝ ለምንድን ነው?+ያለፋታ የምታጠቁኝስ* ለምንድን ነው?+ 23  ምነው ቃሌ በተጻፈ!ምነው በመጽሐፍ ላይ በሰፈረ! 24  ምነው በብረት ብዕርና በእርሳስ፣በዓለቱ ላይ ለዘላለም በተቀረጸ! 25  የሚዋጀኝ*+ ሕያው እንደሆነ በሚገባ አውቃለሁና፤ከጊዜ በኋላ መጥቶ በምድር ላይ ይቆማል። 26  ቆዳዬ በዚህ መንገድ ቢጠፋም፣ገና በሥጋ እያለሁ አምላክን አየዋለሁ፤ 27  እኔ ራሴ እሱን እመለከተዋለሁ፤የሌላ ሰው ዓይን ሳይሆን የገዛ ዓይኖቼ ያዩታል።+ ይሁንና በውስጤ እንደዛልኩ ይሰማኛል!* 28  የችግሩ መንስኤ እኔ ጋ እያለ፣ ‘የምናሳድደው እንዴት ነው?’ ትላላችሁና።+ 29  እናንተ ራሳችሁ ሰይፉን ፍሩ፤+ሰይፉ በበደል ላይ ቅጣት ያመጣልና፤ፈራጅ መኖሩን ልታውቁ ይገባል።”+

የግርጌ ማስታወሻ

ወይም “እኔን የምታበሳጩኝ።” የቃላት መፍቻውን ተመልከት።
ወይም “ሰደባችሁኝ።”
ወይም “ዘመዶቼ ትተውኛል።”
ቃል በቃል “ለማህፀኔም ወንዶች ልጆች።” እኔን የወለደችኝ ማህፀን (የእናቴ ማህፀን) ማለት ነው።
ቃል በቃል “በጥርሴ ቆዳ።”
ቃል በቃል “ሥጋዬን የማትጠግቡትስ።”
ወይም “የሚቤዠኝ።”
ወይም “ኩላሊቴ በውስጤ መሥራት አቆመ።”