ኢዮብ 37:1-24

  • የተፈጥሮ ኃይሎች የአምላክን ታላቅነት ይገልጣሉ (1-24)

    • አምላክ የሰውን ሥራ መግታት ይችላል (7)

    • “የአምላክን ድንቅ ሥራዎች በጥሞና አስብ” (14)

    • “አምላክ ከመረዳት ችሎታችን በላይ ነው” (23)

    • ማንም ሰው ጥበበኛ ነኝ ብሎ አያስብ (24)

37  “ከዚህም የተነሳ ልቤ ይመታል፤ከስፍራውም ይዘላል።   የድምፁን ጉምጉምታ፣ከአፉም የሚወጣውን ነጎድጓድ በጥሞና ስሙ።   ከሰማያት በታች ይልከዋል፤መብረቁንም እስከ ምድር ዳርቻ ድረስ ይሰደዋል።+   ከዚያም በኋላ ድምፅ ያስተጋባል፤ግርማ በተላበሰ ድምፅ ያንጎደጉዳል፤+ድምፁም በሚሰማበት ጊዜ አይከለክለውም።   አምላክ በሚያስደንቅ ሁኔታ በድምፁ ያንጎደጉዳል፤+እኛ መረዳት የማንችላቸውን ታላላቅ ነገሮች ያደርጋል።+   በረዶውን ‘ወደ መሬት ውረድ፣’+ ዶፉን ዝናብም ‘በኃይል ውረድ’ ይለዋልና።+   ሟች የሆነ ሰው ሁሉ ሥራውን እንዲያውቅ፣አምላክ የእያንዳንዱን ሰው ሥራ ያስቆማል።*   የዱር አራዊት ወደ ጎሬአቸው ይገባሉ፤በዋሻዎቻቸውም ውስጥ ይቀመጣሉ።   አውሎ ነፋስ ከማደሪያው ይነፍሳል፤+ቅዝቃዜም ከሰሜን ነፋሳት ይመጣል።+ 10  በአምላክ እስትንፋስ በረዶ ይገኛል፤+የተንጣለሉትም ውኃዎች ግግር በረዶ ይሆናሉ።+ 11  አዎ፣ ደመናትን እርጥበት ያሸክማቸዋል፤በደመናት መካከል መብረቁን ይበትናል፤+ 12  እሱ በመራቸው አቅጣጫ ይሽከረከራሉ፤ሰዎች በሚኖሩበት* የምድር ገጽ ላይ እሱ ያዘዘውን ሁሉ ይፈጽማሉ።+ 13  ለቅጣትም+ ሆነ* ለምድሩ ሲልአሊያም ታማኝ ፍቅር ለማሳየት ይህ እንዲሆን ያደርጋል።+ 14  ኢዮብ ሆይ፣ ይህን ስማ፤ቆም ብለህ የአምላክን ድንቅ ሥራዎች በጥሞና አስብ።+ 15  አምላክ ደመናትን እንዴት እንደሚቆጣጠር፣*ከደመናውም እንዴት መብረቅ እንደሚያበርቅ ታውቃለህ? 16  ደመናት እንዴት እንደሚንሳፈፉ ታውቃለህ?+ እነዚህ፣ እውቀቱ ፍጹም የሆነው አምላክ ድንቅ ሥራዎች ናቸው።+ 17  ምድር በደቡብ ነፋስ ጸጥ ስትል፣ልብስህ የሚሞቀው ለምንድን ነው?+ 18  እንደ ብረት መስተዋት ጠንካራ የሆኑትን ሰማያት፣ከእሱ ጋር ልትዘረጋ* ትችላለህ?+ 19  ለእሱ የምንለውን ንገረን፤ጨለማ ውስጥ ስለሆን መልስ መስጠት አንችልም። 20  እኔ መናገር እንደምፈልግ ለእሱ ማሳወቅ ያስፈልጋል? ወይስ እሱ ሊያውቀው የሚገባ ነገር የተናገረ ሰው አለ?+ 21  በሰማይ ላይ ብርሃን ቢኖርም፣ነፋስ ነፍሶ ደመናቱን ካልበተነ፣ሰዎች ብርሃኑን* ማየት አይችሉም። 22  ከሰሜን ወርቃማ ጨረር ይወጣል፤የአምላክ ግርማ+ አስፈሪ ነው። 23  ሁሉን ቻይ የሆነው አምላክ ከመረዳት ችሎታችን በላይ ነው፤+ኃይሉ ታላቅ ነው፤+ደግሞም ፍትሑንና ታላቅ ጽድቁን አይጥስም።+ 24  ስለዚህ ሰዎች ሊፈሩት ይገባል።+ ጠቢብ ነን ብለው ለሚያስቡ* ሁሉ ሞገስ አያሳይምና።”+

የግርጌ ማስታወሻ

ቃል በቃል “በሰው ሁሉ እጅ ላይ ማኅተም ያኖራል።”
ወይም “ፍሬያማ በሆነው።”
ቃል በቃል “ለበትርም ሆነ።”
ወይም “እንደሚያዝዝ።”
ወይም “ቀጥቅጠህ ልትሠራ።”
የፀሐይን ብርሃን ያመለክታል።
ቃል በቃል “በልብ ጥበበኛ ለሆኑ።”