ዕንባቆም 1:1-17

  • ነቢዩ እርዳታ ለማግኘት ያሰማው ጩኸት (1-4)

    • ‘ይሖዋ ሆይ፣ እስከ መቼ ነው?’ (2)

    • ‘ጭቆናን ለምን ዝም ብለህ ታያለህ?’ (3)

  • የአምላክን ፍርድ ለማስፈጸም መሣሪያ ሆነው ያገለገሉት ከለዳውያን (5-11)

  • ነቢዩ ይሖዋን ተማጸነ (12-17)

    • “አምላኬ ሆይ፣ አንተ አትሞትም” (12)

    • ‘ክፉ የሆነውን ነገር እንዳታይ እጅግ ንጹሕ ነህ’ (13)

1  ነቢዩ ዕንባቆም* በራእይ የተቀበለው መልእክት፦   ይሖዋ ሆይ፣ እርዳታ ለማግኘት ስጮኽ የማትሰማው እስከ መቼ ነው?+ ከግፍ እንድታስጥለኝ ስለምን ጣልቃ የማትገባው እስከ መቼ ነው?*+   ለምን በደል ሲፈጸም እንዳይ ታደርገኛለህ? ጭቆናንስ ለምን ዝም ብለህ ታያለህ? ጥፋትና ግፍ በፊቴ የሚፈጸመው ለምንድን ነው? ጠብና ግጭትስ ለምን በዛ?   ስለዚህ ሕግ ላልቷል፤ፍትሕም ጨርሶ የለም። ክፉው ጻድቁን ከቦታልና፤ከዚህ የተነሳ ፍትሕ ተጣሟል።+   “ብሔራትን እዩ፣ ደግሞም ልብ በሉ! በመገረም ተመልከቱ፤ ተደነቁም፤እናንተ ቢነገራችሁም እንኳ የማታምኑት አንድ ነገርበዘመናችሁ ይከናወናልና።+   እነሆ፣ ጨካኝና ፈጣን የሆነውን ብሔር ይኸውምከለዳውያንን አስነሳለሁና።+ የእነሱ ያልሆኑ ቤቶችን ለመውረስ፣ሰፋፊ የምድር ክፍሎችን ይወራሉ።+   እነሱ አስደንጋጭና አስፈሪ ናቸው። የገዛ ራሳቸውን ፍትሕና ሥልጣን* ያቋቁማሉ።+   ፈረሶቻቸው ከነብር ይልቅ ፈጣኖች ናቸው፤ከሌሊት ተኩላዎችም ይልቅ ጨካኞች ናቸው።+ የጦር ፈረሶቻቸው በፍጥነት ይጋልባሉ፤ፈረሶቻቸው ከሩቅ ስፍራ ይመጣሉ። ለመብላት እንደሚጣደፍ ንስር ተምዘግዝገው ይወርዳሉ።+   ሁሉም ዓመፅ ለመፈጸም ቆርጠው ይመጣሉ።+ እንደ ምሥራቅ ነፋስ ፊታቸውን ያቀናሉ፤+ምርኮኞችንም እንደ አሸዋ ያፍሳሉ። 10  በነገሥታት ይሳለቃሉ፤በከፍተኛ ባለሥልጣናትም ላይ ይስቃሉ።+ በተመሸገ ስፍራ ሁሉ ላይ ይስቃሉ፤+የአፈር ቁልልም ሠርተው ይይዙታል። 11  ከዚያም እንደ ነፋስ ወደ ፊት እየገሰገሱ በምድሪቱ ላይ ያልፋሉ፤ይሁንና በደለኛ ይሆናሉ፤+ምክንያቱም የኃይላቸው ምንጭ አምላካቸው እንደሆነ* ይናገራሉ።”+ 12  ይሖዋ ሆይ፣ አንተ ከዘላለም አንስቶ ያለህ አይደለህም?+ ቅዱስ የሆንከው አምላኬ ሆይ፣ አንተ አትሞትም።*+ ይሖዋ ሆይ፣ እነሱን ፍርድ ለማስፈጸም ሾመሃቸዋል፤ዓለቴ+ ሆይ፣ ቅጣት ለማስፈጸም* አቋቁመሃቸዋል።+ 13  ዓይኖችህ ክፉ የሆነውን ነገር እንዳያዩ እጅግ ንጹሐን ናቸው፤ክፋትንም ዝም ብለህ ማየት አትችልም።+ ታዲያ ከዳተኛውን ዝም ብለህ የምትመለከተው ለምንድን ነው?+ደግሞስ ክፉ ሰው ከእሱ ይልቅ ጻድቅ የሆነውን ሲውጥ ለምን ዝም ትላለህ?+ 14  ሰው እንደ ባሕር ዓሣ፣ገዢም እንደሌላቸው መሬት ለመሬት የሚሳቡ ፍጥረታት እንዲሆን ለምን ትፈቅዳለህ? 15  እሱ* እነዚህን ሁሉ በመንጠቆ ጎትቶ ያወጣል። በመረቡ ይይዛቸዋል፤በዓሣ ማጥመጃ መረቡም ይሰበስባቸዋል። በዚህም እጅግ ሐሴት ያደርጋል።+ 16  በመሆኑም ለመረቡ መሥዋዕት ይሠዋል፤ለዓሣ ማጥመጃ መረቡም መሥዋዕት* ያቀርባል፤በእነሱ የተነሳ ድርሻው በቅባት ተሞልቷል፤ምግቡም ምርጥ ነው። 17  ታዲያ መረቡን ሁልጊዜ ያራግፋል?* ብሔራትንስ ያለርኅራኄ መፍጀቱን ይቀጥላል?+

የግርጌ ማስታወሻ

“አጥብቆ ማቀፍ” የሚል ትርጉም ሊኖረው ይችላል።
ወይም “የማታድነው እስከ መቼ ነው?”
ወይም “ክብር።”
“ኃይላቸው አምላካቸው እንደሆነ” ማለትም ሊሆን ይችላል።
“እኛ አንሞትም” ማለትም ሊሆን ይችላል።
ወይም “እንዲወቅሱ።”
ከለዳዊ የሆነ ጠላትን ያመለክታል።
ወይም “የሚጨስ መሥዋዕት።”
“ሁልጊዜ ሰይፉን ይመዛል?” ማለትም ሊሆን ይችላል።