ዘካርያስ 13:1-9

  • ጣዖታትና ሐሰተኛ ነቢያት ይወገዳሉ (1-6)

    • ሐሰተኛ ነቢያት ኀፍረት ይከናነባሉ (4-6)

  • “እረኛውን ምታ” (7-9)

    • አንድ ሦስተኛው ይነጥራል (9)

13  “በዚያ ቀን፣ ኃጢአታቸውንና ርኩሰታቸውን ለማንጻት ለዳዊት ቤትና ለኢየሩሳሌም ነዋሪዎች የውኃ ጉድጓድ ይቆፈራል።+  “በዚያ ቀን” ይላል የሠራዊት ጌታ ይሖዋ፣ “የጣዖቶቹን ስም ከምድሪቱ ላይ እደመስሳለሁ፤+ እነሱም ዳግመኛ አይታወሱም፤ ደግሞም ነቢያቱንና የርኩሰት መንፈሱን ከምድሪቱ ላይ አስወግዳለሁ።+  አንድ ሰው ዳግመኛ ትንቢት ቢናገር የወለዱት አባትና እናቱ ‘በይሖዋ ስም ሐሰት ስለተናገርክ በሕይወት አትኖርም’ ይሉታል። ደግሞም የወለዱት አባትና እናቱ ትንቢት በመናገሩ ይወጉታል።+  “በዚያ ቀን እያንዳንዱ ነቢይ ትንቢት በሚናገርበት ጊዜ ሁሉ በገዛ ራእዩ ያፍራል፤ ሰዎችንም ለማታለል የነቢያት ዓይነት ፀጉራም ልብስ+ አይለብስም።  ደግሞም እንዲህ ይላል፦ ‘እኔ ነቢይ አይደለሁም። ይልቁንም አራሽ ነኝ፤ ምክንያቱም አንድ ሰው ልጅ ሳለሁ ባሪያ አድርጎ ገዝቶኛል።’  አንድ ሰውም ‘በትከሻዎችህ መካከል* ያሉት ቁስሎች ምንድን ናቸው?’ ብሎ ቢጠይቀው ‘በወዳጆቼ ቤት ሳለሁ የቆሰልኩት ነው’ ይላል።”   “ሰይፍ ሆይ፣ በእረኛዬ+ ይኸውምበወዳጄ ላይ ንቃ” ይላል የሠራዊት ጌታ ይሖዋ። “እረኛውን ምታ፤+ መንጋውም ይበተን፤*+እኔም እጄን ታናናሽ በሆኑት ላይ አዞራለሁ።”   “በምድሪቱም ሁሉ” ይላል ይሖዋ፣“በእሷ ላይ ካለው ሁለት ሦስተኛው ተመትቶ ይጠፋል፤*አንድ ሦስተኛው ግን በውስጧ ይቀራል።   ደግሞም አንድ ሦስተኛው በእሳት ውስጥ እንዲያልፍ አደርጋለሁ፤ብር እንደሚነጥር አነጥራቸዋለሁ፤ወርቅም እንደሚፈተን እፈትናቸዋለሁ።+ እነሱ ስሜን ይጠራሉ፤እኔም እመልስላቸዋለሁ። ‘እነሱ ሕዝቤ ናቸው’ እላለሁ፤+ እነሱ ደግሞ ‘ይሖዋ አምላካችን ነው’ ይላሉ።”

የግርጌ ማስታወሻ

ቃል በቃል “በእጆችህ መካከል።” በደረቱ ወይም በጀርባው ላይ ማለት ነው።
ወይም “በጎቹም ይበተኑ።”
ወይም “ይሞታል።”