አንደኛ ዜና መዋዕል 25:1-31

  • በአምላክ ቤት የሚያገለግሉ ሙዚቀኞችና ዘማሪዎች (1-31)

25  በተጨማሪም ዳዊትና የአገልግሎት ቡድኖቹ አለቆች በበገና፣ በባለ አውታር መሣሪያዎችና+ በሲምባል+ ትንቢት በመናገር እንዲያገለግሉ ከአሳፍ፣ ከሄማን እና ከየዱቱን+ ወንዶች ልጆች መካከል አንዳንዶቹን ለዩ። ይህን አገልግሎት የሚያከናውኑት ኃላፊነት ያላቸው ሰዎች ዝርዝር የሚከተለው ነው፦  ከአሳፍ ወንዶች ልጆች መካከል ዛኩር፣ ዮሴፍ፣ ነታንያህ እና አሼርዔላ፤ እነዚህ በአሳፍ አመራር ሥር ያሉ የአሳፍ ወንዶች ልጆች ሲሆኑ በንጉሡ አመራር ሥር ሆነው ትንቢት ይናገሩ ነበር።  ከየዱቱን፣+ የየዱቱን ወንዶች ልጆች፦ ጎዶልያስ፣ ጸሪ፣ የሻያህ፣ ሺምአይ፣ ሃሻብያህ እና ማቲትያህ፤+ እነዚህ ስድስቱ በአባታቸው በየዱቱን አመራር ሥር ሲሆኑ ይሖዋን እያመሰገኑና እያወደሱ+ በበገና ትንቢት ይናገሩ ነበር።  ከሄማን፣+ የሄማን ወንዶች ልጆች፦ ቡቂያ፣ ማታንያህ፣ ዑዚኤል፣ ሸቡኤል፣* የሪሞት፣ ሃናንያህ፣ ሃናኒ፣ ኤሊዓታህ፣ ጊዳልቲ፣ ሮማምቲኤዘር፣ ዮሽበቃሻ፣ ማሎቲ፣ ሆቲር እና ማሃዚዮት።  እነዚህ ሁሉ የሄማን ወንዶች ልጆች ነበሩ፤ እሱም ለአምላክ ክብር ያመጣ ዘንድ* የእውነተኛውን አምላክ ቃል የሚገልጽ የንጉሡ ባለ ራእይ ነበር፤ እውነተኛውም አምላክ ለሄማን 14 ወንዶች ልጆችና 3 ሴቶች ልጆች ሰጠው።  እነዚህ ሁሉ በእውነተኛው አምላክ ቤት ለሚቀርበው አገልግሎት በአባታቸው አመራር ሥር ሆነው በሲምባል፣ በባለ አውታር መሣሪያዎችና በበገና+ በይሖዋ ቤት ይዘምሩ ነበር። አሳፍ፣ የዱቱን እና ሄማን በንጉሡ አመራር ሥር ነበሩ።  የእነሱና ለይሖዋ በሚቀርበው መዝሙር የሠለጠኑት ወንድሞቻቸው ይኸውም በዚህ የተካኑት ሰዎች አጠቃላይ ቁጥር 288 ነበር።  በመሆኑም ከሥራቸው ጋር በተያያዘ ታናሽም ሆነ ታላቅ፣ በሙያው የተካነም ሆነ ተማሪ ሳይባል ሁሉም ዕጣ+ ተጣጣሉ።  የመጀመሪያው ዕጣ ለአሳፍ ልጅ ለዮሴፍ+ ወጣ፤ ሁለተኛው ለጎዶልያስ+ ወጣ (እሱና ወንድሞቹ እንዲሁም ወንዶች ልጆቹ 12 ነበሩ)፤ 10  ሦስተኛው ለዛኩር፣+ ለወንዶች ልጆቹና ለወንድሞቹ ወጣ፤ ቁጥራቸውም 12 ነበር፤ 11  አራተኛው ለይጽሪ፣ ለወንዶች ልጆቹና ለወንድሞቹ ወጣ፤ ቁጥራቸውም 12 ነበር፤ 12  አምስተኛው ለነታንያህ፣+ ለወንዶች ልጆቹና ለወንድሞቹ ወጣ፤ ቁጥራቸውም 12 ነበር፤ 13  ስድስተኛው ለቡቂያ፣ ለወንዶች ልጆቹና ለወንድሞቹ ወጣ፤ ቁጥራቸውም 12 ነበር፤ 14  ሰባተኛው ለየሳርኤላ፣ ለወንዶች ልጆቹና ለወንድሞቹ ወጣ፤ ቁጥራቸውም 12 ነበር፤ 15  ስምንተኛው ለየሻያህ፣ ለወንዶች ልጆቹና ለወንድሞቹ ወጣ፤ ቁጥራቸውም 12 ነበር፤ 16  ዘጠነኛው ለማታንያህ፣ ለወንዶች ልጆቹና ለወንድሞቹ ወጣ፤ ቁጥራቸውም 12 ነበር፤ 17  አሥረኛው ለሺምአይ፣ ለወንዶች ልጆቹና ለወንድሞቹ ወጣ፤ ቁጥራቸውም 12 ነበር፤ 18  አሥራ አንደኛው ለአዛርዔል፣ ለወንዶች ልጆቹና ለወንድሞቹ ወጣ፤ ቁጥራቸውም 12 ነበር፤ 19  አሥራ ሁለተኛው ለሃሻብያህ፣ ለወንዶች ልጆቹና ለወንድሞቹ ወጣ፤ ቁጥራቸውም 12 ነበር፤ 20  አሥራ ሦስተኛው ለሹባኤል፣+ ለወንዶች ልጆቹና ለወንድሞቹ ወጣ፤ ቁጥራቸውም 12 ነበር፤ 21  አሥራ አራተኛው ለማቲትያህ፣ ለወንዶች ልጆቹና ለወንድሞቹ ወጣ፤ ቁጥራቸውም 12 ነበር፤ 22  አሥራ አምስተኛው ለየሬሞት፣ ለወንዶች ልጆቹና ለወንድሞቹ ወጣ፤ ቁጥራቸውም 12 ነበር፤ 23  አሥራ ስድስተኛው ለሃናንያህ፣ ለወንዶች ልጆቹና ለወንድሞቹ ወጣ፤ ቁጥራቸውም 12 ነበር፤ 24  አሥራ ሰባተኛው ለዮሽበቃሻ፣ ለወንዶች ልጆቹና ለወንድሞቹ ወጣ፤ ቁጥራቸውም 12 ነበር፤ 25  አሥራ ስምንተኛው ለሃናኒ፣ ለወንዶች ልጆቹና ለወንድሞቹ ወጣ፤ ቁጥራቸውም 12 ነበር፤ 26  አሥራ ዘጠነኛው ለማሎቲ፣ ለወንዶች ልጆቹና ለወንድሞቹ ወጣ፤ ቁጥራቸውም 12 ነበር፤ 27  ሃያኛው ለኤሊዓታህ፣ ለወንዶች ልጆቹና ለወንድሞቹ ወጣ፤ ቁጥራቸውም 12 ነበር፤ 28  ሃያ አንደኛው ለሆቲር፣ ለወንዶች ልጆቹና ለወንድሞቹ ወጣ፤ ቁጥራቸውም 12 ነበር፤ 29  ሃያ ሁለተኛው ለጊዳልቲ፣+ ለወንዶች ልጆቹና ለወንድሞቹ ወጣ፤ ቁጥራቸውም 12 ነበር፤ 30  ሃያ ሦስተኛው ለማሃዚዮት፣+ ለወንዶች ልጆቹና ለወንድሞቹ ወጣ፤ ቁጥራቸውም 12 ነበር፤ 31  ሃያ አራተኛው ለሮማምቲኤዘር፣+ ለወንዶች ልጆቹና ለወንድሞቹ ወጣ፤ ቁጥራቸውም 12 ነበር።

የግርጌ ማስታወሻ

በ1ዜና 24:20 እና 25:20 ላይ ሹባኤል ተብሎም ተጠርቷል።
ቃል በቃል “ቀንዱን ከፍ ያደርግ ዘንድ።”