በቀጥታ ወደ ዋናው ጉዳይ ግባ

በቀጥታ ወደ ርዕስ ማውጫው ሂድ

ጥያቄ 3

መጽሐፍ ቅዱስን የጻፈው ማን ነው?

 “ሙሴ የይሖዋን ቃል ሁሉ በጽሑፍ አሰፈረ።”

ዘፀአት 24:4

 “ዳንኤል በአልጋው ላይ ተኝቶ ሳለ ሕልምና ራእዮች አየ። ከዚያም ያየውን ሕልም ጻፈ፤ ጉዳዩንም በዝርዝር አሰፈረ።”

ዳንኤል 7:1

 “የአምላክን ቃል ከእኛ በሰማችሁ ጊዜ እንደ ሰው ቃል ሳይሆን እንደ አምላክ ቃል አድርጋችሁ ተቀብላችሁታል፤ ደግሞም የአምላክ ቃል ነው።”

1 ተሰሎንቄ 2:13

 “ቅዱሳን መጻሕፍት ሁሉ በአምላክ መንፈስ መሪነት የተጻፉ ናቸው፤ እንዲሁም ለማስተማር . . . ይጠቅማሉ።”

2 ጢሞቴዎስ 3:16

 “መቼም ቢሆን ትንቢት በሰው ፈቃድ አልመጣምና፤ ከዚህ ይልቅ ሰዎች ከአምላክ የተቀበሉትን ትንቢት በመንፈስ ቅዱስ ተገፋፍተው ተናገሩ።”

2 ጴጥሮስ 1:21